وُجُوهٞ يَوۡمَئِذٖ نَّاضِرَةٌ

ፊቶች በዚያ ቀን አብሪዎች ናቸው፡፡


إِلَىٰ رَبِّهَا نَاظِرَةٞ

ወደ ጌታቸው ተመልካቾች ናቸው፡፡


وَوُجُوهٞ يَوۡمَئِذِۭ بَاسِرَةٞ

ፊቶችም በዚያ ቀን ጨፍጋጊዎች ናቸው፡፡


تَظُنُّ أَن يُفۡعَلَ بِهَا فَاقِرَةٞ

በርሳቸውም ዐደጋ እንደሚሠራባቸው ያረጋግጣሉ፡፡


كَلَّآ إِذَا بَلَغَتِ ٱلتَّرَاقِيَ

ንቁ (ነፍስ) ብሪዎችን በደረሰች ጊዜ፤


وَقِيلَ مَنۡۜ رَاقٖ

«አሻሪው ማነው?» በተባለም ጊዜ፡፡


وَظَنَّ أَنَّهُ ٱلۡفِرَاقُ

(ሕመምተኛው) እርሱ (የሰፈረበት ነገር ከዚህ ዓለም) መልለየት መኾኑን ባረጋገጠም ጊዜ፡፡


وَٱلۡتَفَّتِ ٱلسَّاقُ بِٱلسَّاقِ

ባትም በባት በተጣበቀች ጊዜ፡፡


إِلَىٰ رَبِّكَ يَوۡمَئِذٍ ٱلۡمَسَاقُ

በዚያ ቀን መነዳቱ ወደ ጌታህ (ፍርድ) ነው፡፡


فَلَا صَدَّقَ وَلَا صَلَّىٰ

አላመነምም አልሰገደምም፡፡


وَلَٰكِن كَذَّبَ وَتَوَلَّىٰ

ግን አስተባበለ፤ (ከእምነት) ዞረም፡፡


ثُمَّ ذَهَبَ إِلَىٰٓ أَهۡلِهِۦ يَتَمَطَّىٰٓ

ከዚያም እየተንጎባለለ ወደ ቤተሰቡ ኼደ፡፡



الصفحة التالية
Icon