لِيَوۡمِ ٱلۡفَصۡلِ

ለመለያው ቀን (በተባለ ጊዜ፤ በፍጡሮች መካከል ይፈረዳል)፡፡


وَمَآ أَدۡرَىٰكَ مَا يَوۡمُ ٱلۡفَصۡلِ

የመለያውም ቀን ምን እንደኾነ ምን አሳወቀህ?


وَيۡلٞ يَوۡمَئِذٖ لِّلۡمُكَذِّبِينَ

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡


أَلَمۡ نُهۡلِكِ ٱلۡأَوَّلِينَ

የፊተኞቹን (ሕዝቦች) አላጠፋንምን?


ثُمَّ نُتۡبِعُهُمُ ٱلۡأٓخِرِينَ

ከዚያም የኋለኞቹን እናስከትላቸዋለን፡፡


كَذَٰلِكَ نَفۡعَلُ بِٱلۡمُجۡرِمِينَ

በአመጸኞች ሁሉ እንደዚሁ እንሠራለን፡፡


وَيۡلٞ يَوۡمَئِذٖ لِّلۡمُكَذِّبِينَ

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡


أَلَمۡ نَخۡلُقكُّم مِّن مَّآءٖ مَّهِينٖ

ከደካማ ውሃ አልፈጠርናችሁምን?


فَجَعَلۡنَٰهُ فِي قَرَارٖ مَّكِينٍ

በተጠበቀ መርጊያ ውስጥም (በማሕፀን) አደረግነው፡፡


إِلَىٰ قَدَرٖ مَّعۡلُومٖ

እስከ ታወቀ ልክ ድረስ፡፡ መጠንነውም፤ ምን ያማርንም


فَقَدَرۡنَا فَنِعۡمَ ٱلۡقَٰدِرُونَ

መጣኞች ነን!


وَيۡلٞ يَوۡمَئِذٖ لِّلۡمُكَذِّبِينَ

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡



الصفحة التالية
Icon