فَإِنَّمَا هِيَ زَجۡرَةٞ وَٰحِدَةٞ

እርሷም አንዲት ጩኸት ብቻ ናት፡፡


فَإِذَا هُم بِٱلسَّاهِرَةِ

ወዲያውኑም እነርሱ እንቅልፍ በሌለባት (ምድር) ላይ ይኾናሉ፡፡


هَلۡ أَتَىٰكَ حَدِيثُ مُوسَىٰٓ

የሙሳ ወሬ መጣልህን?


إِذۡ نَادَىٰهُ رَبُّهُۥ بِٱلۡوَادِ ٱلۡمُقَدَّسِ طُوًى

ጌታው በተቀደሰው ሸለቆ በጡዋ በጠራው ጊዜ፤


ٱذۡهَبۡ إِلَىٰ فِرۡعَوۡنَ إِنَّهُۥ طَغَىٰ

ወደ ፈርዖን ኺድ፡፡ እርሱ ወሰን አልፏልና፡፡


فَقُلۡ هَل لَّكَ إِلَىٰٓ أَن تَزَكَّىٰ

በለውም፡- «ወደ መጥራራትህ ላንተ (መንገድ) አለህን?»


وَأَهۡدِيَكَ إِلَىٰ رَبِّكَ فَتَخۡشَىٰ

«ወደ ጌታህም ልመራህ ትፈራውም ዘንድ፤ (መንገድ አለህን?)» አለው፡፡


فَأَرَىٰهُ ٱلۡأٓيَةَ ٱلۡكُبۡرَىٰ

ታላቂቱንም ተዓምር አሳየው፡፡


فَكَذَّبَ وَعَصَىٰ

አስተባበለም፤ አመጸም፡፡


ثُمَّ أَدۡبَرَ يَسۡعَىٰ

ከዚያም (ለማጥፋት) የሚተጋ ኾኖ ዞረ፡፡


فَحَشَرَ فَنَادَىٰ

(ሰራዊቶቹን) ሰበሰበም፤ ተጣራም፡፡


فَقَالَ أَنَا۠ رَبُّكُمُ ٱلۡأَعۡلَىٰ

አለም፡- «እኔ ታላቁ ጌታችሁ ነኝ፡፡»



الصفحة التالية
Icon