فَأَخَذَهُ ٱللَّهُ نَكَالَ ٱلۡأٓخِرَةِ وَٱلۡأُولَىٰٓ

አላህም በኋለኛይቱና በፊተኛይቱ (ቃል) ቅጣት ያዘው፡፡


إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَعِبۡرَةٗ لِّمَن يَخۡشَىٰٓ

በዚህ ውስጥ ለሚፈራ ሰው በእርግጥ መገምገሚያ አለበት፡፡


ءَأَنتُمۡ أَشَدُّ خَلۡقًا أَمِ ٱلسَّمَآءُۚ بَنَىٰهَا

ባፈጣጠር እናንተ ይበልጥ የበረታችሁ ናችሁን? ወይንስ ሰማይ? (አላህ) ገነባት፡፡


رَفَعَ سَمۡكَهَا فَسَوَّىٰهَا

ከፍታዋን አጓነ፤ አስተካከላትም፡፡


وَأَغۡطَشَ لَيۡلَهَا وَأَخۡرَجَ ضُحَىٰهَا

ሌሊቷንም አጨለመ፡፡ ቀንዋንም ገለጸ፡፡


وَٱلۡأَرۡضَ بَعۡدَ ذَٰلِكَ دَحَىٰهَآ

ምድርንም ከዚህ በኋላ ዘረጋት፡፡


أَخۡرَجَ مِنۡهَا مَآءَهَا وَمَرۡعَىٰهَا

ውሃዋንና ግጦሿን ከእርሷ አወጣ፡፡


وَٱلۡجِبَالَ أَرۡسَىٰهَا

ጋራዎችንም አደላደላቸው፡፡


مَتَٰعٗا لَّكُمۡ وَلِأَنۡعَٰمِكُمۡ

ለእናንተና ለእንስሶቻችሁ መጣቀሚያ ይኾን ዘንድ (ይህን አደረገ)፡፡


فَإِذَا جَآءَتِ ٱلطَّآمَّةُ ٱلۡكُبۡرَىٰ

ታላቂቱም መዐት በመጣች ጊዜ፣


يَوۡمَ يَتَذَكَّرُ ٱلۡإِنسَٰنُ مَا سَعَىٰ

ሰው ሁሉ የሠራውን በሚያስታውስበት ቀን፣



الصفحة التالية
Icon