فِي صُحُفٖ مُّكَرَّمَةٖ

በተከበሩ ጽሑፎች ውስጥ ነው፡፡


مَّرۡفُوعَةٖ مُّطَهَّرَةِۭ

ከፍ በተደረገች ንጹሕ በተደረገች (ጽሑፍ ውስጥ ነው)፡፡


بِأَيۡدِي سَفَرَةٖ

በጸሐፊዎቹ (መላእክት) እጆች (ንጹሕ የተደረገች)፡፡


كِرَامِۭ بَرَرَةٖ

የተከበሩና ታዛዦች በኾኑት (ጸሐፊዎች እጆች)፡፡


قُتِلَ ٱلۡإِنسَٰنُ مَآ أَكۡفَرَهُۥ

ሰው ተረገመ፤ ምን ከሓዲ አደረገው?


مِنۡ أَيِّ شَيۡءٍ خَلَقَهُۥ

(ጌታው) በምን ነገር ፈጠረው? (አያስብምን?)


مِن نُّطۡفَةٍ خَلَقَهُۥ فَقَدَّرَهُۥ

ከፍትወት ጠብታ ፈጠረው፤ መጠነውም፡፡


ثُمَّ ٱلسَّبِيلَ يَسَّرَهُۥ

ከዚያም (መውጫ) መንገዱን አገራው፡፡


ثُمَّ أَمَاتَهُۥ فَأَقۡبَرَهُۥ

ከዚያም ገደለው፤ እንዲቀበርም አደረገው፡፡


ثُمَّ إِذَا شَآءَ أَنشَرَهُۥ

ከዚያም (ማንሳቱን) በሻ ጊዜ ያስነሳዋል፡፡


كَلَّا لَمَّا يَقۡضِ مَآ أَمَرَهُۥ

በእውነት ያንን (ጌታው) ያዘዘውን ገና አልፈጸመም፡፡


فَلۡيَنظُرِ ٱلۡإِنسَٰنُ إِلَىٰ طَعَامِهِۦٓ

ሰውም ወደ ምግቡ ይመልከት፡፡



الصفحة التالية
Icon