وَإِذَا ٱلۡجَنَّةُ أُزۡلِفَتۡ

ገነትም በተቀረበች ጊዜ፤


عَلِمَتۡ نَفۡسٞ مَّآ أَحۡضَرَتۡ

ነፍስ ሁሉ (ከሥራ) ያቀረበችውን ታውቃለች፤


فَلَآ أُقۡسِمُ بِٱلۡخُنَّسِ

ተመላሾችም በኾኑት (ዐዋድያት) እምላለሁ፡፡


ٱلۡجَوَارِ ٱلۡكُنَّسِ

ኺያጆች ገቢዎች በኾኑት (ከዋክብት)፡፡


وَٱلَّيۡلِ إِذَا عَسۡعَسَ

በሌሊቱም (ጨለማውን) በጠነሰሰ ጊዜ፤


وَٱلصُّبۡحِ إِذَا تَنَفَّسَ

በንጋቱም (በብርሃን) በተነፈሰ ጊዜ፤ (እምላለሁ)፡፡


إِنَّهُۥ لَقَوۡلُ رَسُولٖ كَرِيمٖ

እርሱ (ቁርኣን) የክቡር መልክተኛ ቃል ነው፡፡


ذِي قُوَّةٍ عِندَ ذِي ٱلۡعَرۡشِ مَكِينٖ

የኀይል ባለቤት በዙፋኑ ባለ ቤት ዘንድ ባለሟል የኾነ፡፡


مُّطَاعٖ ثَمَّ أَمِينٖ

በዚያ ስፍራ ትእዛዙ ተሰሚ፤ ታማኝ የኾነ (መልክተኛ ቃል) ነው፡፡


وَمَا صَاحِبُكُم بِمَجۡنُونٖ

ነቢያችሁም በፍጹም ዕብድ አይደለም፡፡


وَلَقَدۡ رَءَاهُ بِٱلۡأُفُقِ ٱلۡمُبِينِ

በግልጹ አድማስም በእርግጥ አይቶታል፡፡


وَمَا هُوَ عَلَى ٱلۡغَيۡبِ بِضَنِينٖ

እርሱም በሩቁ ወሬ ላይ ሰሳች (ንፉግ) አይደለም፡፡



الصفحة التالية
Icon