وَٱلذَّـٰرِيَٰتِ ذَرۡوٗا

መበተንን በታኞች በኾኑት (ነፋሶች)፡፡


فَٱلۡحَٰمِلَٰتِ وِقۡرٗا

ከባድ (ዝናምን) ተሸካሚዎች በኾኑትም (ደመናዎች)፡፡


فَٱلۡجَٰرِيَٰتِ يُسۡرٗا

ገር (መንሻለልን) ተንሻላዮች በኾኑትም (መርከቦች)፡፡


فَٱلۡمُقَسِّمَٰتِ أَمۡرًا

ነገርን ሁሉ አከፋፋዮች በኾኑትም (መላእክት) እምላለሁ፡፡


إِنَّمَا تُوعَدُونَ لَصَادِقٞ

የምትቀጠሩት (ትንሣኤ) እውነት ነው፡፡


وَإِنَّ ٱلدِّينَ لَوَٰقِعٞ

(እንደየሥራው) ዋጋን ማግኘትም፤ ኋኝ ነው፤ (የማይቀር ነው)፡፡


وَٱلسَّمَآءِ ذَاتِ ٱلۡحُبُكِ

የ(ከዋክብት) መንገዶች ባለቤት በኾነችው ሰማይ እምላለሁ፡፡


إِنَّكُمۡ لَفِي قَوۡلٖ مُّخۡتَلِفٖ

እናንተ (የመካ ሰዎች) በተለያየ ቃል ውስጥ ናችሁ፡፡


يُؤۡفَكُ عَنۡهُ مَنۡ أُفِكَ

ከርሱ የሚዝዞር ሰው ይዝዞራል፡፡


قُتِلَ ٱلۡخَرَّـٰصُونَ

በግምት የሚናገሩ ውሸታሞች ተረገሙ፡፡


ٱلَّذِينَ هُمۡ فِي غَمۡرَةٖ سَاهُونَ

እነዚያ እነርሱ በሚሸፍን ስሕተተ ውስጥ ዘንጊዎች የኾኑት፡፡



الصفحة التالية
Icon