وَٱلنَّجۡمِ إِذَا هَوَىٰ

በኮከብ እምላለሁ በወደቀ (በገባ) ጊዜ፡፡


مَا ضَلَّ صَاحِبُكُمۡ وَمَا غَوَىٰ

ነቢያችሁ (ሙሐመድ) አልተሳሳተም፤ አልጠመመምም፡፡


وَمَا يَنطِقُ عَنِ ٱلۡهَوَىٰٓ

ከልብ ወለድም አይናገርም፡፡


إِنۡ هُوَ إِلَّا وَحۡيٞ يُوحَىٰ

እርሱ (ንግግሩ) የሚወርረድ ራእይ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡


عَلَّمَهُۥ شَدِيدُ ٱلۡقُوَىٰ

ኀይሎቹ ብርቱው (መልአክ) አስተማረው፡፡


ذُو مِرَّةٖ فَٱسۡتَوَىٰ

የዕውቀት ባለቤት የኾነው (አስተማረው፤ በተፈጥሮ ቅርጹ ኾኖ በአየር ላይ) ተደላደለም፡፡


وَهُوَ بِٱلۡأُفُقِ ٱلۡأَعۡلَىٰ

እርሱ በላይኛው አድማስ ኾኖ፡፡


ثُمَّ دَنَا فَتَدَلَّىٰ

ከዚያም ቀረበ፤ ወረደም፡፡


فَكَانَ قَابَ قَوۡسَيۡنِ أَوۡ أَدۡنَىٰ

(ከእርሱ) የሁለት ደጋኖች ጫፍ ያህል ወይም (ከዚህ) ይበልጥ የቀረበ ኾነም፡፡


فَأَوۡحَىٰٓ إِلَىٰ عَبۡدِهِۦ مَآ أَوۡحَىٰ

ወደ ባሪያውም (አላህ) ያወረደውን አወረደ፡፡


مَا كَذَبَ ٱلۡفُؤَادُ مَا رَأَىٰٓ

(ነቢዩም በዓይኑ) ያየውን ልቡ አልዋሸም፡፡



الصفحة التالية
Icon