نٓۚ وَٱلۡقَلَمِ وَمَا يَسۡطُرُونَ

ነ.(ኑን)፤ በብርእ እምላለሁ በዚያም (መልአኮች) በሚጽፉት፡፡


مَآ أَنتَ بِنِعۡمَةِ رَبِّكَ بِمَجۡنُونٖ

አንተ በጌታህ ጸጋ የተጎናጸፍክ ስትኾን ዕብድ አይደለህም፡፡


وَإِنَّ لَكَ لَأَجۡرًا غَيۡرَ مَمۡنُونٖ

ላንተም (ከጌታህ) የማይቋረጥ ዋጋ በእርግጥ አልለህ፡፡


وَإِنَّكَ لَعَلَىٰ خُلُقٍ عَظِيمٖ

አንተም በታላቅ ጠባይ ላይ ነህ፡፡


فَسَتُبۡصِرُ وَيُبۡصِرُونَ

ወደፊትም ታያለህ፤ ያያሉም፡፡


بِأَييِّكُمُ ٱلۡمَفۡتُونُ

ዕብደት በማንኛችሁ እንዳልለ፡፡


إِنَّ رَبَّكَ هُوَ أَعۡلَمُ بِمَن ضَلَّ عَن سَبِيلِهِۦ وَهُوَ أَعۡلَمُ بِٱلۡمُهۡتَدِينَ

ጌታህ እርሱ ከመንገዱ የተሳሳተውን ሰው ዐዋቂ ነው፡፡ እርሱም ተመሪዎቹን ዐዋቂ ነው፡፡


فَلَا تُطِعِ ٱلۡمُكَذِّبِينَ

ለአስተባባዮችም አትታዝዙ፡፡


وَدُّواْ لَوۡ تُدۡهِنُ فَيُدۡهِنُونَ

ብትመሳሰላቸውና ቢመሳሰሉህ ተመኙ፡፡


وَلَا تُطِعۡ كُلَّ حَلَّافٖ مَّهِينٍ

ወራዳንም ሁሉ አትታዘዝ፡፡


هَمَّازٖ مَّشَّآءِۭ بِنَمِيمٖ

ሰውን አነዋሪንና በማሳበቅ ኼያጅን፡፡



الصفحة التالية
Icon