سَأَلَ سَآئِلُۢ بِعَذَابٖ وَاقِعٖ

ወዳቂ ከኾነው ቅጣት ጠያቂ ጠየቀ፡፡


لِّلۡكَٰفِرِينَ لَيۡسَ لَهُۥ دَافِعٞ

በከሓዲዎች ላይ (ወዳቂ ከኾነው) ለእርሱ መላሽ የለውም፡፡


مِّنَ ٱللَّهِ ذِي ٱلۡمَعَارِجِ

የ(ሰማያት) መሰላሎች ባለቤት ከኾነው አላህ (መላሽ የለውም)፡፡


تَعۡرُجُ ٱلۡمَلَـٰٓئِكَةُ وَٱلرُّوحُ إِلَيۡهِ فِي يَوۡمٖ كَانَ مِقۡدَارُهُۥ خَمۡسِينَ أَلۡفَ سَنَةٖ

መላእክቱና መንፈሱም ልኩ አምሳ ሺሕ ዓመት በኾነ ቀን ውስጥ ወደእርሱ ያርጋሉ፤ (ይወጣሉ)፡፡


فَٱصۡبِرۡ صَبۡرٗا جَمِيلًا

መልካምንም ትዕግስት ታገሥ፡፡


إِنَّهُمۡ يَرَوۡنَهُۥ بَعِيدٗا

እነርሱ (ያንን ቀን) ሩቅ አድርገው ያዩታል፡፡


وَنَرَىٰهُ قَرِيبٗا

እኛም ቅርብ ኾኖ እናየዋለን፡፡


يَوۡمَ تَكُونُ ٱلسَّمَآءُ كَٱلۡمُهۡلِ

ሰማይ እንደ ዘይት አተላ በምትኾንበት ቀን፡፡


وَتَكُونُ ٱلۡجِبَالُ كَٱلۡعِهۡنِ

ጋራዎችም በተለያዩ ቀለማት እንደ ተነከረ ሱፍ (ነፋስ እንደሚያበረው) በሚኾኑበት ቀን፡፡


وَلَا يَسۡـَٔلُ حَمِيمٌ حَمِيمٗا

ዘመድም ዘመድን በማይጠይቅበት ቀን፤ (መላሽ የለውም)፡፡



الصفحة التالية
Icon