لَآ أُقۡسِمُ بِيَوۡمِ ٱلۡقِيَٰمَةِ

(ነገሩ ከሓዲዎች እንደሚሉት) አይደለም፡፡ በትንሣኤ ቀን እምላለሁ፡፡


وَلَآ أُقۡسِمُ بِٱلنَّفۡسِ ٱللَّوَّامَةِ

(ራሷን) ወቃሽ በኾነች ነፍስም እምላለሁ፡፡ (በእርግጥ ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡


أَيَحۡسَبُ ٱلۡإِنسَٰنُ أَلَّن نَّجۡمَعَ عِظَامَهُۥ

ሰው አጥንቶቹን አለመሰብሰባችንን ያስባልን?


بَلَىٰ قَٰدِرِينَ عَلَىٰٓ أَن نُّسَوِّيَ بَنَانَهُۥ

አይደለም ጣቶቹን (ፊት እንደ ነበሩ) በማስተካከል ላይ ቻዮች ስንኾን (እንሰበስባቸዋለን)፡፡


بَلۡ يُرِيدُ ٱلۡإِنسَٰنُ لِيَفۡجُرَ أَمَامَهُۥ

ይልቁንም ሰው በፊቱ ባለው ነገር (በትንሣኤ) ሊያስተባብል ይፈልጋል፡፡


يَسۡـَٔلُ أَيَّانَ يَوۡمُ ٱلۡقِيَٰمَةِ

«የትንሣኤው ቀን መቼ ነው?» ሲል ይጠይቃል፡፡


فَإِذَا بَرِقَ ٱلۡبَصَرُ

ዓይንም በዋለለ ጊዜ፡፡


وَخَسَفَ ٱلۡقَمَرُ

ጨረቃም በጨለመ ጊዜ፡፡


وَجُمِعَ ٱلشَّمۡسُ وَٱلۡقَمَرُ

ፀሐይና ጨረቃም በተሰበሰቡ ጊዜ፡፡


يَقُولُ ٱلۡإِنسَٰنُ يَوۡمَئِذٍ أَيۡنَ ٱلۡمَفَرُّ

«ሰው በዚያ ቀን መሸሻው የት ነው?» ይላል፡፡



الصفحة التالية
Icon