وَٱلۡمُرۡسَلَٰتِ عُرۡفٗا

ተከታታይ ኾነው በተላኩት፣


فَٱلۡعَٰصِفَٰتِ عَصۡفٗا

በኀይል መንፈስን ነፋሾች በኾኑትም፣


وَٱلنَّـٰشِرَٰتِ نَشۡرٗا

መበተንን በታኞች በኾኑትም፤ (ነፋሶች)፣


فَٱلۡفَٰرِقَٰتِ فَرۡقٗا

መለየትን ለይዎች በኾኑትም፣


فَٱلۡمُلۡقِيَٰتِ ذِكۡرًا

መገሠጫን (ወደ ነቢያት) ጣይዎች በኾኑትም፣


عُذۡرًا أَوۡ نُذۡرًا

ምክንያትን ለማስወገድ ወይም ለማስፈራራት (ጣይዎች በኾኑት መላእክት) እምላለሁ፡፡


إِنَّمَا تُوعَدُونَ لَوَٰقِعٞ

ያ የምትስፈራሩበት (ትንሣኤ) በእርግጥ ኋኝ ነው፡፡


فَإِذَا ٱلنُّجُومُ طُمِسَتۡ

ከዋክብትም (ብርሃንዋ) በታበሰች ጊዜ፡፡


وَإِذَا ٱلسَّمَآءُ فُرِجَتۡ

ሰማይም በተከፈተች ጊዜ፡፡


وَإِذَا ٱلۡجِبَالُ نُسِفَتۡ

ጋራዎችም በተንኮተኮቱ ጊዜ፡፡


وَإِذَا ٱلرُّسُلُ أُقِّتَتۡ

መልክተኞቹም ወቅት በተደረገላቸው ጊዜ፡፡


لِأَيِّ يَوۡمٍ أُجِّلَتۡ

ለየትኛው ቀን ተቀጠሩ (የሚባል ሲኾን)፤



الصفحة التالية
Icon