عَمَّ يَتَسَآءَلُونَ

ከምን ነገር ይጠያየቃሉ?


عَنِ ٱلنَّبَإِ ٱلۡعَظِيمِ

ከታላቁ ዜና (ከቁርኣን ይጠያየቃሉ)፡፡


ٱلَّذِي هُمۡ فِيهِ مُخۡتَلِفُونَ

ከዚያ እነርሱ በእርሱ የተለያዩበት ከኾነው፡፡


كَلَّا سَيَعۡلَمُونَ

ይከልከሉ፤ ወደፊት (የሚደርስበቸውን) በእርግጥ ያውቃሉ፡፡


ثُمَّ كَلَّا سَيَعۡلَمُونَ

ከዚያም ይከልከሉ፤ ወደፊት ያውቃሉ፡፡


أَلَمۡ نَجۡعَلِ ٱلۡأَرۡضَ مِهَٰدٗا

ምድርን ምንጣፍ አላደረግንምን?


وَٱلۡجِبَالَ أَوۡتَادٗا

ጋራዎችንም ችካሎች አላደረግንምን?


وَخَلَقۡنَٰكُمۡ أَزۡوَٰجٗا

ብዙ ዓይነቶችም አድርገን ፈጠርናችሁ፡፡


وَجَعَلۡنَا نَوۡمَكُمۡ سُبَاتٗا

እንቅልፋችሁንም ዕረፍት አደረግን፡፡


وَجَعَلۡنَا ٱلَّيۡلَ لِبَاسٗا

ሌሊቱንም ልባስ አደረግን፡፡


وَجَعَلۡنَا ٱلنَّهَارَ مَعَاشٗا

ቀኑንም (ለኑሮ) መስሪያ አደረግን፡፡


وَبَنَيۡنَا فَوۡقَكُمۡ سَبۡعٗا شِدَادٗا

ከበላያችሁም ሰባትን ብርቱዎች (ሰማያት) ገነባን፡፡



الصفحة التالية
Icon