وَٱلنَّـٰزِعَٰتِ غَرۡقٗا

በኃይል አውጪዎች በኾኑት፤


وَٱلنَّـٰشِطَٰتِ نَشۡطٗا

በቀስታ መምዘዝንም መዘዦች በኾኑት፤


وَٱلسَّـٰبِحَٰتِ سَبۡحٗا

መዋኘትም ዋኚዎች በኾኑት፤


فَٱلسَّـٰبِقَٰتِ سَبۡقٗا

መቅደምንም ቀዳሚዎች በኾኑት፤


فَٱلۡمُدَبِّرَٰتِ أَمۡرٗا

ነገርንም አስተናባሪዎች በኾኑት (መላእክት) እምላለሁ፡፡ (በእርግጥ ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡


يَوۡمَ تَرۡجُفُ ٱلرَّاجِفَةُ

ተርገፍጋፊይቱ (ምድር) በምትርገፈገፍበት ቀን፤


تَتۡبَعُهَا ٱلرَّادِفَةُ

ለጣቂይቱ የምትከተላት ስትኾን (ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡


قُلُوبٞ يَوۡمَئِذٖ وَاجِفَةٌ

በዚያ ቀን ልቦች ተሸባሪዎች ናቸው፡፡


أَبۡصَٰرُهَا خَٰشِعَةٞ

ዓይኖቻቸው ተዋራጆች (አቀርቃሪዎች) ናቸው፡፡


يَقُولُونَ أَءِنَّا لَمَرۡدُودُونَ فِي ٱلۡحَافِرَةِ

«እኛ ወደ መጀመሪያይቱ ኹነታ ተመላሾች ነን?» ይላሉ፡፡


أَءِذَا كُنَّا عِظَٰمٗا نَّخِرَةٗ

«የበሰበሱ አጥንቶች በኾን ጊዜ (እንቀሰቀሳለን?)»


قَالُواْ تِلۡكَ إِذٗا كَرَّةٌ خَاسِرَةٞ

«ይህቺ ያን ጊዜ ባለ ከሳራ መመለስ ናት» ይላሉ፡፡



الصفحة التالية
Icon