عَبَسَ وَتَوَلَّىٰٓ

ፊቱን አጨፈገገ፤ ዞረም፡፡


أَن جَآءَهُ ٱلۡأَعۡمَىٰ

ዕውሩ ስለ መጣው፡፡


وَمَا يُدۡرِيكَ لَعَلَّهُۥ يَزَّكَّىٰٓ

ምን ያሳውቅሃል? (ከኀጢአቶቹ) ሊጥራራ ይከጀላል፡፡


أَوۡ يَذَّكَّرُ فَتَنفَعَهُ ٱلذِّكۡرَىٰٓ

ወይም ሊገሠጽ ግሠጼይቱም ልትጠቅመው (ይከጀላል)፡፡


أَمَّا مَنِ ٱسۡتَغۡنَىٰ

የተብቃቃው ሰውማ፤


فَأَنتَ لَهُۥ تَصَدَّىٰ

አንተ ለእርሱ (ለእምነቱ በመጓጓት) በፈገግታ ትቀበለዋለህ፡፡


وَمَا عَلَيۡكَ أَلَّا يَزَّكَّىٰ

ባይጥራራ (ባያምን) ባንተ ላይ ምንም የሌለብህ ስትኾን፡፡


وَأَمَّا مَن جَآءَكَ يَسۡعَىٰ

እየገሰገሰ የመጣህ ሰውማ፤


وَهُوَ يَخۡشَىٰ

እርሱ (አላህን) የሚፈራ ሲኾን፤


فَأَنتَ عَنۡهُ تَلَهَّىٰ

አንተ ከእርሱ ትዝዘናጋለህ፡፡


كَلَّآ إِنَّهَا تَذۡكِرَةٞ

ተከልከል፡፡ እርሷ ማስገንዘቢያ ናት፡፡


فَمَن شَآءَ ذَكَرَهُۥ

የሻም ሰው (ቁርኣኑን) ያስታውሰዋል፡፡



الصفحة التالية
Icon