إِذَا ٱلسَّمَآءُ ٱنفَطَرَتۡ

ሰማይ በተሰነጠቀች ጊዜ፤


وَإِذَا ٱلۡكَوَاكِبُ ٱنتَثَرَتۡ

ከዋክብትም ተበታትነው በወደቁ ጊዜ፤


وَإِذَا ٱلۡبِحَارُ فُجِّرَتۡ

ባሕሮችም በተከፈቱና በተደበላለቁ ጊዜ፤


وَإِذَا ٱلۡقُبُورُ بُعۡثِرَتۡ

መቃብሮችም በተገለባበጡና (ሙታን) በተነሱ ጊዜ፤


عَلِمَتۡ نَفۡسٞ مَّا قَدَّمَتۡ وَأَخَّرَتۡ

ማንኛይቱም ነፍስ ያስቀደመችውንና ያቆየችውን ታውቃለች፡፡


يَـٰٓأَيُّهَا ٱلۡإِنسَٰنُ مَا غَرَّكَ بِرَبِّكَ ٱلۡكَرِيمِ

አንተ ሰው ሆይ! በቸሩ ጌታህ ምን አታለለህ?


ٱلَّذِي خَلَقَكَ فَسَوَّىٰكَ فَعَدَلَكَ

በዚያ በፈጠረህ አካለ ሙሉም ባደረገህ ባስተካከለህም፡፡


فِيٓ أَيِّ صُورَةٖ مَّا شَآءَ رَكَّبَكَ

በማንኛውም በሻው ቅርፅ በገጣጠመህ (ጌታህ ምን አታለለህ)፡፡


كَلَّا بَلۡ تُكَذِّبُونَ بِٱلدِّينِ

ተከልከሉ፤ በእውነቱ በፍርዱ ቀን ታስተባብላላችሁ፡፡


وَإِنَّ عَلَيۡكُمۡ لَحَٰفِظِينَ

በእናንተ ላይ ተጠባባቂዎች ያሉባችሁ፤ ስትኾኑ፤


كِرَامٗا كَٰتِبِينَ

የተከበሩ ጸሐፊዎች የኾኑ፤ (ተጠባባቂዎች)፡፡



الصفحة التالية
Icon