وَٱلسَّمَآءِ ذَاتِ ٱلۡبُرُوجِ

የቡርጆች ባለቤት በኾነችው ሰማይ እምላለሁ፡፡


وَٱلۡيَوۡمِ ٱلۡمَوۡعُودِ

በተቀጠረው ቀንም፤


وَشَاهِدٖ وَمَشۡهُودٖ

በተጣጅና በሚጣዱትም፤ (እምላለሁ)፡፡


قُتِلَ أَصۡحَٰبُ ٱلۡأُخۡدُودِ

የጉድቡ ባለቤቶች ተረገሙ፡፡


ٱلنَّارِ ذَاتِ ٱلۡوَقُودِ

የማገዶ ባለቤት የኾነቺው እሳት (ባለቤቶች)፡፡


إِذۡ هُمۡ عَلَيۡهَا قُعُودٞ

እነርሱ በርሷ (አፋፍ) ላይ ተቀማጮች በኾኑ ጊዜ፤ (ተረገሙ)፡፡


وَهُمۡ عَلَىٰ مَا يَفۡعَلُونَ بِٱلۡمُؤۡمِنِينَ شُهُودٞ

እነርሱም በምእምናኖቹ በሚሠሩት (ማሰቃየት) ላይ መስካሪዎች ናቸው፡፡


وَمَا نَقَمُواْ مِنۡهُمۡ إِلَّآ أَن يُؤۡمِنُواْ بِٱللَّهِ ٱلۡعَزِيزِ ٱلۡحَمِيدِ

ከእነርሱም በአላህ አሸናፊው፣ ምስጉኑ በኾነው (ጌታ) ማመናቸውን እንጅ ሌላ ምንም አልጠሉም፡፡


ٱلَّذِي لَهُۥ مُلۡكُ ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلۡأَرۡضِۚ وَٱللَّهُ عَلَىٰ كُلِّ شَيۡءٖ شَهِيدٌ

በእዚያ የሰማያትና የምድር ንግሥና ለእርሱ ብቻ በኾነው (አላህ ማመናቸውን)፡፡ አላህም በነገሩ ሁሉ ላይ መስካሪ ነው፡፡


إِنَّ ٱلَّذِينَ فَتَنُواْ ٱلۡمُؤۡمِنِينَ وَٱلۡمُؤۡمِنَٰتِ ثُمَّ لَمۡ يَتُوبُواْ فَلَهُمۡ عَذَابُ جَهَنَّمَ وَلَهُمۡ عَذَابُ ٱلۡحَرِيقِ

እነዚያ ምእምንንና ምእምናትን ያሰቃዩ፣ ከዚያም ያልተጸጸቱ ለእነርሱ የገሀነም ቅጣት አልላቸው፡፡ ለእነርሱም የመቃጠሉ ስቃይ አልላቸው፡፡



الصفحة التالية
Icon