وَٱلسَّمَآءِ وَٱلطَّارِقِ

በሰማዩ በሌሊት መጪውም እምላለሁ፡፡


وَمَآ أَدۡرَىٰكَ مَا ٱلطَّارِقُ

የሌሊት መጪውም ምን እንደ ኾነ ምን አሳወቀህ?


ٱلنَّجۡمُ ٱلثَّاقِبُ

ጨለማን ቀዳጁ ኮከብ ነው፡፡


إِن كُلُّ نَفۡسٖ لَّمَّا عَلَيۡهَا حَافِظٞ

ነፍስ ሁሉ በእርሷ ላይ ጠባቂ ያለባት እንጅ ሌላ አይደለችም፡፡


فَلۡيَنظُرِ ٱلۡإِنسَٰنُ مِمَّ خُلِقَ

ሰውም ከምን እንደተፈጠረ ይመልከት፡፡


خُلِقَ مِن مَّآءٖ دَافِقٖ

ከተስፈንጣሪ ውሃ ተፈጠረ፡፡


يَخۡرُجُ مِنۢ بَيۡنِ ٱلصُّلۡبِ وَٱلتَّرَآئِبِ

ከጀርባና ከእርግብግብቶች መካከል የሚወጣ ከኾነ (ውሃ)፡፡


إِنَّهُۥ عَلَىٰ رَجۡعِهِۦ لَقَادِرٞ

እርሱ (አላህ) በመመለሱ ላይ በእርግጥ ቻይ ነው፡፡


يَوۡمَ تُبۡلَى ٱلسَّرَآئِرُ

ምስጢሮች በሚገለጡበት ቀን፡፡


فَمَا لَهُۥ مِن قُوَّةٖ وَلَا نَاصِرٖ

ለእርሱም (ለሰው) ኀይልና ረዳት ምንም የለውም፡፡


وَٱلسَّمَآءِ ذَاتِ ٱلرَّجۡعِ

የመመለስ ባለቤት በኾነችው ሰማይም እምላለሁ፡፡



الصفحة التالية
Icon