سَبِّحِ ٱسۡمَ رَبِّكَ ٱلۡأَعۡلَى

ከሁሉ በላይ የኾነውን ጌታህን ስም አሞግሥ፡፡


ٱلَّذِي خَلَقَ فَسَوَّىٰ

የዚያን (ሁሉን ነገር) የፈጠረውን ያስተካከለውንም፡፡


وَٱلَّذِي قَدَّرَ فَهَدَىٰ

የዚያንም የወሰነውን፡፡ (ለተፈጠረለት ነገር) የመራውንም፡፡


وَٱلَّذِيٓ أَخۡرَجَ ٱلۡمَرۡعَىٰ

የዚያንም ግጦሽን (ለምለም አድርጎ) ያወጣውን፡፡


فَجَعَلَهُۥ غُثَآءً أَحۡوَىٰ

(ከዚያ) ደረቅ ጥቁር ያደረገውንም (አምላክ ስም አሞግስ)፡፡


سَنُقۡرِئُكَ فَلَا تَنسَىٰٓ

(ቁርኣንን) በእርግጥ እናስነብብሃለን፤ አትረሳምም፡፡


إِلَّا مَا شَآءَ ٱللَّهُۚ إِنَّهُۥ يَعۡلَمُ ٱلۡجَهۡرَ وَمَا يَخۡفَىٰ

አላህ ከሻው ነገር በስተቀር፡፡ እርሱ ግልጹን የሚሸሸገውንም ሁሉ ያውቃልና፡፡


وَنُيَسِّرُكَ لِلۡيُسۡرَىٰ

ለገሪቱም (ሕግጋት) እንገጥምሃለን፡፡


فَذَكِّرۡ إِن نَّفَعَتِ ٱلذِّكۡرَىٰ

ግሣጼይቱ ብትጠቅም (ሰዎችን) ገሥጽም፡፡


سَيَذَّكَّرُ مَن يَخۡشَىٰ

(አላህን) የሚፈራ ሰው በእርግጥ ይገሠጻል፡፡


وَيَتَجَنَّبُهَا ٱلۡأَشۡقَى

መናጢውም ይርቃታል፡፡



الصفحة التالية
Icon