هَلۡ أَتَىٰكَ حَدِيثُ ٱلۡغَٰشِيَةِ

የሸፋኝቱ (ትንሣኤ) ወሬ መጣህን?


وُجُوهٞ يَوۡمَئِذٍ خَٰشِعَةٌ

ፊቶች በዚያ ቀን ተዋራጆች ናቸው፡፡


عَامِلَةٞ نَّاصِبَةٞ

ሠሪዎች ለፊዎች ናቸው፡፡


تَصۡلَىٰ نَارًا حَامِيَةٗ

ተኳሳን እሳት ይገባሉ፡፡


تُسۡقَىٰ مِنۡ عَيۡنٍ ءَانِيَةٖ

በጣም ከፈላች ምንጭ ይጋታሉ፡፡


لَّيۡسَ لَهُمۡ طَعَامٌ إِلَّا مِن ضَرِيعٖ

ለእነርሱ ዶሪዕ ከሚባል (እሾሃም) ዛፍ እንጅ ሌላ ምግብ የላቸውም፡፡


لَّا يُسۡمِنُ وَلَا يُغۡنِي مِن جُوعٖ

የማያሰባ ከረኃብም የማያብቃቃ ከኾነው፡፡


وُجُوهٞ يَوۡمَئِذٖ نَّاعِمَةٞ

ፊቶች በዚያ ቀን ተቀማጣዮች ናቸው፡፡


لِّسَعۡيِهَا رَاضِيَةٞ

ለሥራቸው ተደሳቾች ናቸው፡፡


فِي جَنَّةٍ عَالِيَةٖ

በከፍተኛ ገነት ውስጥ ናቸው፡፡


لَّا تَسۡمَعُ فِيهَا لَٰغِيَةٗ

በውስጧ ውድቅን ነገር አይሰሙም፡፡


فِيهَا عَيۡنٞ جَارِيَةٞ

በውስጧ ፈሳሾች ምንጮች አልሉ፡፡



الصفحة التالية
Icon