ٱقۡرَأۡ بِٱسۡمِ رَبِّكَ ٱلَّذِي خَلَقَ

አንብብ በዚያ (ሁሉን) በፈጠረው ጌታህ ስም፡፡


خَلَقَ ٱلۡإِنسَٰنَ مِنۡ عَلَقٍ

ሰውን ከረጋ ደም በፈጠረው (ጌታህ ስም)፡፡


ٱقۡرَأۡ وَرَبُّكَ ٱلۡأَكۡرَمُ

አንብብ፤ ጌታህ በጣም ቸር ሲኾን፤


ٱلَّذِي عَلَّمَ بِٱلۡقَلَمِ

ያ በብርዕ ያስተማረ፡፡


عَلَّمَ ٱلۡإِنسَٰنَ مَا لَمۡ يَعۡلَمۡ

ሰውን ያላወቀውን ሁሉ ያሳወቀ ሲኾን፡፡


كَلَّآ إِنَّ ٱلۡإِنسَٰنَ لَيَطۡغَىٰٓ

በእውነቱ ሰው ወሰንን ያልፋል፡፡


أَن رَّءَاهُ ٱسۡتَغۡنَىٰٓ

ራሱን የተብቃቃ (ባለ ሀብት) ኾኖ ለማየቱ፡፡


إِنَّ إِلَىٰ رَبِّكَ ٱلرُّجۡعَىٰٓ

መመለሻው ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡


أَرَءَيۡتَ ٱلَّذِي يَنۡهَىٰ

አየህን? ያንን የሚከለክለውን፡፡


عَبۡدًا إِذَا صَلَّىٰٓ

ባሪያን በሰገደ ጊዜ፤


أَرَءَيۡتَ إِن كَانَ عَلَى ٱلۡهُدَىٰٓ

አየህን? ንገረኝ (ተከልካዩ) በትክክለኛ መንገድ ላይ ቢኾን፤


أَوۡ أَمَرَ بِٱلتَّقۡوَىٰٓ

ወይም (ፈጣሪውን) በመፍራት ቢያዝ፤



الصفحة التالية
Icon