ﰉ
                    surah.translation
            .
            
    
                                    من تأليف: 
                                            محمد صادق ومحمد الثاني حبيب
                                                            .
                                                
            ﰡ
በሌሊቱ እምላለሁ (በጨለማው) በሚሸፍን ጊዜ፡፡
                                                                        በቀኑም፤ በተገለጸ ጊዜ፡፡
                                                                        ወንድንና ሴትን በፈጠረውም (አምላክ እምላለሁ)፡፡
                                                                        ሥራችሁ በእርግጥ የተለያየ ነው፡፡
                                                                        የሰጠ ሰውማ ጌታውን የፈራም፡፡
                                                                        
                                                                                                                
                                    ﯘﯙ
                                    ﰅ
                                                                        
                    በመልካሚቱም (እምነት) ያረጋገጠ፤
                                                                        
                                                                                                                
                                    ﯛﯜ
                                    ﰆ
                                                                        
                    ለገሪቱ ሥራ እናዘጋጀዋለን፡፡
                                                                        የሰሰተ ሰውማ የተብቃቃም፤ (በራሱ የተመካ)፤
                                                                        
                                                                                                                
                                    ﯣﯤ
                                    ﰈ
                                                                        
                    በመልካሚቱ (እምነት) ያሰተባበለም፤
                                                                        
                                                                                                                
                                    ﭑﭒ
                                    ﰉ
                                                                        
                    ለክፉይቱ ሥራ እናዘጋጀዋለን፡፡
                                                                        በወደቀም ጊዜ ገንዘቡ ከእርሱ ምንም አይጠቅመውም፡፡
                                                                        ቅኑን መንገድ መግለጽ በእኛ ላይ አለብን፡፡
                                                                        መጨረሻይቱም መጀመሪያይቱም ዓለም የእኛ ናቸው፡፡
                                                                        የምትንቀለቀልንም እሳት አስጠነቀቅኳችሁ (በላቸው)፡፡
                                                                        ከጠማማ በቀር ሌላ የማይገባት የኾነችን፡፡
                                                                        ያ ያስተባበለና ከትዕዛዝ የሸሸው፡፡
                                                                        
                                                                                                                
                                    ﭱﭲ
                                    ﰐ
                                                                        
                    አላህን በጣም ፈሪውም በእርግጥ ይርቃታል፡፡
                                                                        ያ የሚጥራራ ኾኖ ገንዘቡን (ለድኾች) የሚሰጠው፡፡
                                                                        ለአንድም ሰው እርሱ ዘንድ የምትመለስ ውለታ የለችም፡፡
                                                                        ግን የታላቅ ጌታውን ውዴታ ለመፈለግ (ይህንን ሠራ)፡፡
                                                                        
                                                                                                                
                                    ﮆﮇ
                                    ﰔ
                                                                        
                    ወደፊትም በእርግጥ ይደሰታል፡፡