surah.translation .


በዝሆኑ ባለቤቶች ጌታህ እንዴት እንደሠራ አላወቅህምን?

ተንኮላቸውን በጥፋት ውስጥ (ከንቱ) አላደረገምን? (አድርጓል)፡፡

በእነርሱም ላይ መንጎች የኾኑን ዎፎች ላከ፡፡

ከተጠበሰ ጭቃ በኾነ ድንጋይ የምትወረውርባቸው የኾነችን፤ (አዕዋፍ)፡፡

ቅጠሉ እንደ ተበላ አዝመራም አደረጋቸው፡፡