ترجمة معاني سورة الحجر باللغة الأمهرية من كتاب الترجمة الأمهرية
محمد صادق
آية رقم 1
አ.ለ.ረ (አሊፍ ላም ራ) ይህች (አናቅጽ) ከመጽሐፉ አንቀጾችና ገላጭ ከኾነው ቁርኣን ናት፡፡
آية رقم 2
እነዚያ የካዱት (በትንሣኤ ቀን) ሙስሊሞች በኾኑ ኖሩ በብዛት ይመኛሉ፡፡
آية رقم 3
ተዋቸው ይብሉ፤ ይጠቀሙም፡፡ ተስፋም ያዘናጋቸው፡፡ በእርግጥም (መጥፎ ፍጻሜያቸውን) ያውቃሉ፡፡
آية رقم 4
ማንኛይቱንም ከተማ ለእርሷ የተወሰነ መጽሐፍ (ጊዜያት) ያላት ኾና እንጂ አላጠፋንም፡፡
آية رقم 5
ማንኛይቱም ሕዝብ ጊዜዋን ምንም አትቀድምም፡፡ (ከእርሱ) አይቆዩምም፡፡
آية رقم 6
«አንተ ያ በእርሱ ላይ ቁርኣን የተወረደለት ሆይ! አንተ በእርግጥ ዕብድ ነህ» አሉም፡፡
آية رقم 7
«ከእውነተኞቹ እንደ ኾንክ በመላእክት (መስካሪ) ለምን አትመጣንም» (አሉ)፡፡
آية رقم 8
መላእክትን በእውነት (በቅጣት) እንጂ አናወርድም፡፡ ያን ጊዜም የሚቆዩ አይደሉም፡፡
آية رقم 9
እኛ ቁርኣንን እኛው አወረድነው፡፡ እኛም ለእርሱ ጠባቂዎቹ ነን፡፡
آية رقم 10
ከአንተም በፊት በነበሩት በመጀመሪያዎቹ ሕዝቦች ውስጥ (መልክተኞችን) በእርግጥ ልከናል፡፡
آية رقم 11
ማንኛውም መልእክተኛ በእርሱ የሚያላግጡበት ኾነው እንጅ አይመጣቸውም ነበር፡፡
آية رقم 12
ﮰﮱﯓﯔﯕ
ﯖ
እንደዚሁ (ማስተባበልን) በአመጸኞቹ ልቦች ውስጥ እናገባዋለን፡፡
آية رقم 13
በእርሱ አያምኑበትም፡፡ የቀድሞዎቹም ድርጊት በእርግጥ አልፋለች፤ (እንደጠፉ ይጠፋሉ)፡፡
آية رقم 14
በእነርሱም ላይ ከሰማይ ደጃፍን በከፈትንላቸውና በእርሱ ሲወጡ በዋሉ ኖሮ፤
آية رقم 15
«የተዘጉት ዓይኖቻችን ናቸው፡፡ እንዲያውም እኛ የተደገመብን ሰዎች ነን» ባሉ ነበር፡፡
آية رقم 16
በሰማይም ላይ ቡርጆችን በእርግጥ አድርገናል፡፡ ለተመልካቾችም (በከዋክብት) አጊጠናታል፡፡
آية رقم 17
ﭙﭚﭛﭜﭝ
ﭞ
ከተባረረ ሰይጣንም ሁሉ ጠብቀናታል፡፡
آية رقم 18
ግን (ወሬ) መስማትን የሚሰርቅ ወዲየውኑ አብሪ ችቦ ይከተለዋል፡፡ (ያቃጥለዋል)፡፡
آية رقم 19
ምድርንም ዘረጋናት፡፡ በውስጧም ኮረብታዎችን ጣልናባት፡፡ በውስጧም (የተለካን) በቃይ ሁሉ አበቀልንባት፡፡
آية رقم 20
በእርሷም ውስጥ ለእናንተ መኖሪያዎችንና ለእርሱ መጋቢዎቹ ያልኾናችሁትንም (እንስሳትን) አደረግንላችሁ፡፡
آية رقم 21
መካዚኖቹም (መክፈቻቸው) እኛ ዘንድ ያልሆነ ምንም ነገር የለም፡፡ በተወሰነም ልክ እንጂ አናወርደውም፡፡
آية رقم 22
ነፋሶችንም (ደመናን) ተሸካሚዎች አድርገን ላክን፡፡ ከሰማይም (ከደመና) ዝናብን አወረድን፡፡ እርሱንም አጠጣናችሁ፡፡ እናንተም ለእርሱ አድላቢዎች አይደላችሁም፡፡
آية رقم 23
ﮕﮖﮗﮘﮙﮚ
ﮛ
እኛም ሕያው የምናደርግና የምንገድል እኛው ብቻ ነን፡፡ እኛም (ፍጡርን ሁሉ ) የምንወርስ (ቀሪ) ነን፡፡
آية رقم 24
ከእናንተም ተቀዳሚዎቹን በእርግጥ ዐውቀናል፡፡ ወደ ኋላም ቀሪዎቹን በእርግጥ ዐውቀናል፡፡
آية رقم 25
ጌታህም እርሱ ይሰበስባችኋል፡፡ እርሱ ጥበበኛ ዐዋቂ ነውና፡፡
آية رقم 26
ሰውንም ከሚቅጨለጨል ሸክላ ከሚገማ ጥቁር ጭቃ በእርግጥ ፈጠርነው፡፡
آية رقم 27
ጃንንም (ከሰው) በፊት ከእሳት ነበልባል ፈጠርነው፡፡
آية رقم 28
ጌታህም ለመላእክት ባለጊዜ (አስታውስ)፡፡ እኔ ሰውን ከሚቅጨለጨል ሸክላ ከሚገማ ጭቃ እፈጥራለሁ፡፡
آية رقم 29
(ፍጥረቱን) ባስተካከልኩትና በውስጡ ከመንፈሴ በነፋሁበትም ጊዜ ለእርሱ ሰጋጆች ኾናችሁ ውደቁ፡፡
آية رقم 30
ﯶﯷﯸﯹ
ﯺ
መላእክትም መላውም ተሰብስበው ሰገዱ፡፡
آية رقم 31
ኢብሊስ (ዲያብሎስ) ብቻ ሲቀር፡፡ ከሰጋጆቹ ጋር ከመኾን እንቢ አለ፡፡
آية رقم 32
(አላህም) «ኢብሊስ ሆይ! ከሰጋጆቹ ጋር የማትኾን ላንተ ምን ምክንያት አለህ» አለው፡፡
آية رقم 33
«ከሚቅጨለጨል ሸክላ ከግም ጭቃ ለፈጠርከው ሰው ልሰግድ አይገባኝም» አለ፡፡
آية رقم 34
ﭦﭧﭨﭩﭪ
ﭫ
(አላህ) አለው «ከርሷም ውጣ፡፡ አንተ የተባረርክ እርጉም ነህና፡፡»
آية رقم 35
ﭬﭭﭮﭯﭰﭱ
ﭲ
«ባንተ ላይም እስከ ፍርዱ ቀን ድረስ እርግማን አለብህ፡፡»
آية رقم 36
ﭳﭴﭵﭶﭷﭸ
ﭹ
«ጌታዬ ሆይ! እንግዲውያስ (ሰዎች) እስከሚቀሰቀሱበት ቀን ድረስ አቆየኝ» አለ፡፡
آية رقم 37
ﭺﭻﭼﭽ
ﭾ
(አላህም) አለ «አንተ ከሚቆዩት ነህ፡፡
آية رقم 38
ﭿﮀﮁﮂ
ﮃ
«እስከታወቀው ወቅት ቀን ድረስ፡፡»
آية رقم 39
(ኢብሊስ) አለ «ጌታዬ ሆይ! እኔን በማጥመምህ ይኹንብኝ ለነርሱ በምድር ላይ (ኀጢአትን) እሸልምላቸዋለሁ፡፡ ሁሉንም አጠማቸዋለሁም፡፡»
آية رقم 40
ﮏﮐﮑﮒ
ﮓ
«ከነርሱ ፍጹሞቹ ባሮችህ ብቻ ሲቀሩ፡፡»
آية رقم 41
ﮔﮕﮖﮗﮘ
ﮙ
(አላህም) አለ «ይህ በእኔ ላይ (መጠበቁ የተገባ) ቀጥተኛ መንገድ ነው፡፡»
آية رقم 42
«እነሆ ባሮቼ በእነሱ ላይ ላንተ ስልጣን የለህም፡፡ ከጠማሞቹ የተከተለህ ሰው ብቻ ሲቀር፡፡»
آية رقم 43
ﮦﮧﮨﮩ
ﮪ
«ገሀነምም (ለርሱና ለተከተሉት) ለመላውም በእርግጥ ቀጠሯቸው ናት፡፡
آية رقم 44
«ለእርሷ ሰባት ደጃፎች አሏት፡፡ ለየደጀፉም ሁሉ ከእነሱ የተከፈለ ፋንታ አለ፡፡
آية رقم 45
ﯕﯖﯗﯘﯙ
ﯚ
«እነዚያ (ከኀጢአት) የተጠነቀቁት በአትክልቶችና በምንጮች ውስጥ ናቸው፡፡
آية رقم 46
ﯛﯜﯝ
ﯞ
«ጸጥተኞች ኾናችሁ በሰላም ግቧት (ይባላሉ)፡፡
آية رقم 47
«ባልጋዎችም ላይ ፊት ለፊት የሚቅጣጩ ወንድማማቾች ኾነው በደረቶቻቸው ውስጥ ከቂም ያለውን ሁሉ እናስወግዳለን፡፡
آية رقم 48
«በእርሷም ውስጥ ድካም አይነካቸውም፡፡ እነሱም ከእርሷ የሚወጡ አይደሉም፡፡»
آية رقم 49
ባሮቼን እኔ መሓሪው አዛኙ እኔው ብቻ መኾኔን ንገራቸው፡፡
آية رقم 50
ﯻﯼﯽﯾﯿ
ﰀ
ቅጣቴም እርሱ አሳማሚ ቅጣት መኾኑን (ንገራቸው)፡፡
آية رقم 51
ﰁﰂﰃﰄ
ﰅ
ከኢብራሂም እንግዶችም (ወሬ) ንገራቸው፡፡
آية رقم 52
በእርሱ ላይ በገቡና ሰላም ባሉት ጊዜ የኾነውን (አስታውስ)፡፡ (እርሱም) «እኛ ከእናንተ ፈሪዎች ነን» አላቸው፡፡
آية رقم 53
«አትፍራ፤ እኛ ዐዋቂ በኾነ ወንድ ልጅ እናበስርሃለን» አሉት፡፡
آية رقم 54
«እርጅና የደረሰብኝ ከመኾኔ ጋር አበሰራችሁኝን በምን ታበስሩኛላችሁ» አለ፡፡
آية رقم 55
«በእውነት አበሰርንህ፡፡ ከተሰፋ ቆራጮችም አትኹን» አሉ፡፡
آية رقم 56
«ከጠማማዎችም በስተቀር ከጌታው እዝነት ተስፋን የሚቆርጥ ማነው» አለ፡፡
آية رقم 57
ﭽﭾﭿﮀﮁ
ﮂ
«እናንተ መልክተኞች ሆይ! ኧረ ለመኾኑ ነገራችሁ ምንድን ነው» አለ፡፡
آية رقم 58
ﮃﮄﮅﮆﮇﮈ
ﮉ
«እኛ አመጸኞች ወደ ኾኑ ሕዝቦች ተልከናል» አሉት፡፡
آية رقم 59
ﮊﮋﮌﮍﮎﮏ
ﮐ
«የሉጥ ቤተሰቦች ብቻ ሲቀሩ፡፡ (እነርሱን) እኛ ሁላቸውንም በእርግጥ የምናድናቸው ነን፡፡
آية رقم 60
ﮑﮒﮓﮔﮕﮖ
ﮗ
«ሚስቱ ብቻ ስትቀር፡፡ እርሷን (በቅጣቱ ውስጥ) ከሚቀሩት መኾኗን ወሰነናል» (አሉ)፡፡
آية رقم 61
ﮘﮙﮚﮛﮜ
ﮝ
መልክተኞቹም የሉጥን ቤተሰቦች በመጡባቸው ጊዜ፤
آية رقم 62
ﮞﮟﮠﮡ
ﮢ
(ሉጥ) «እናንተ የተሳታችሁ ሕዝቦች ናችሁ» አላቸው፡፡
آية رقم 63
«አይደለም እኛ ሕዝቦችህ በርሱ ይጠራጠሩበት በነበሩት ቅጣት መጣንህ» አሉት፡፡
آية رقم 64
ﮫﮬﮭﮮ
ﮯ
«እውነትንም ይዘን መጣንህ፡፡ እኛም በእርግጥ እውነተኞች ነን፡፡
آية رقم 65
ከቤተሰብህም ጋር በሌሊቱ ከፊል ኺድ፡፡ ከኋላቸውም ተከተል፡፡ ከእናንተም አንድም ሰው ወደ ኋላው አይገላመጥ፡፡ ወደ ታዘዛችሁበትም ስፍራ እለፉ» (አሉት)፡፡
آية رقم 66
ወደርሱም ያንን ትእዛዝ አወረድን፡፡ (እርሱም) የእነዚህ (ሕዝቦች) መጨረሻ ያነጉ ሲኾኑ (ሥራቸው) መቆረጥ ነው፡፡
آية رقم 67
ﯪﯫﯬﯭ
ﯮ
የከተማይቱም ሰዎች የሚበሳሰሩ ኾነው መጡ፡፡
آية رقم 68
ﯯﯰﯱﯲﯳﯴ
ﯵ
(ሉጥም) አለ «እነዚህ እንግዶቼ ናቸውና አታጋልጡኝ፡፡
آية رقم 69
ﯶﯷﯸﯹ
ﯺ
«አላህንም ፍሩ፤ አታሳፍሩኝም፡፡»
آية رقم 70
ﯻﯼﯽﯾﯿ
ﰀ
«ከዓለማት (ማንንም እንዳታስተናግድ) አልከለከልንህምን» አሉት፡፡
آية رقم 71
ﭑﭒﭓﭔﭕﭖ
ﭗ
(ሉጥም) «እነኝህ ሴቶች ልጆቼ ናቸው፡፡ ሠሪዎች ብትኾኑ (አግቧቸው)» አለ፡፡
آية رقم 72
ﭘﭙﭚﭛﭜ
ﭝ
በዕድሜህ እንምላለን እነሱ በእርግጥ በስከራቸው ውስጥ ይዋልላሉ፡፡
آية رقم 73
ﭞﭟﭠ
ﭡ
ጩኸቲቱም ፀሐይ የወጣችባቸው ሲኾኑ ያዘቻቸው፡፡
آية رقم 74
ላይዋንም ከታችዋ አደረግን፡፡ በእነሱም ላይ የሸክላ ደንጊያዎችን አዘነብንባቸው፡፡
آية رقم 75
ﭫﭬﭭﭮﭯ
ﭰ
በዚህ ውስጥ ለተመልካቾች በእርግጥ መገምገሚያዎች አሉበት፡፡
آية رقم 76
ﭱﭲﭳ
ﭴ
እሷም (ከተማይቱ) በቀጥታ መንገድ ላይ ናት፡፡
آية رقم 77
ﭵﭶﭷﭸﭹ
ﭺ
በዚህ ውስጥ በእርግጥ ለምእምናን መገሰጫ አለ፡፡
آية رقم 78
ﭻﭼﭽﭾﭿ
ﮀ
እነሆ የአይከት ሰዎችም በእርግጥ በዳዮች ነበሩ፤
آية رقم 79
ﮁﮂﮃﮄﮅ
ﮆ
ከነሱም ተበቀልን ሁለቱም (የሉጥና የአይከት ሕዝቦች ከተሞች) በእርግጥ በግልጽ መንገድ ላይ ናቸው፡፡
آية رقم 80
ﮇﮈﮉﮊﮋ
ﮌ
የሒጅርም ሰዎች መልክተኞቹን በእርግጥ አስተባበሉ፡፡
آية رقم 81
ﮍﮎﮏﮐﮑ
ﮒ
ተዓምራታችንንም ሰጠናቸው፡፡ ከእርሷም ዘንጊዎች ነበሩ፡፡
آية رقم 82
ﮓﮔﮕﮖﮗﮘ
ﮙ
ከኮረብታዎችም ቤቶችን ጸጥተኞች ኾነው ይጠርቡ ነበር፡፡
آية رقم 83
ﮚﮛﮜ
ﮝ
ያነጉም ሲኾኑ ጩኸት ያዘቻቸው፤ (ወደሙ)፡፡
آية رقم 84
ﮞﮟﮠﮡﮢﮣ
ﮤ
ይሠሩትም የነበሩት ሕንጻ ምንም አልጠቀማቸውም፡፡
آية رقم 85
ሰማያትንና ምድርንም በመካከላቸው ያለውንም ሁሉ በእውነት እንጂ (በላግጣ) አልፈጠርንም፡፡ ሰዓቲቱም በእርግጥ መጪ ናት፡፡ መልካምንም ይቅርታ አድርግላቸው፡፡
آية رقم 86
ﯗﯘﯙﯚﯛ
ﯜ
ጌታህ እርሱ (ያልነበረን) ፈጣሪው ዐዋቂው ነው፡፡
آية رقم 87
ከሚደጋገሙ የኾኑን ሰባትንና ታላቁንም ቁርኣን (በሙሉ) በእርግጥ ሰጠንህ፡፡
آية رقم 88
ከእነርሱ (ከከሓዲዎች) ብዙዎችን ወገኖች በእርሱ ወደ አጣቀምንበት ጸጋ ዓይኖችህን አትዘርጋ፡፡ በእነሱም ላይ (ባያምኑ) አትዘን፡፡ ክንፍህንም ለምእምናን አለዝብ፡፡
آية رقم 89
ﯵﯶﯷﯸﯹ
ﯺ
በልም «እኔ ግልጽ አስፈራሪው እኔ ነኝ፡፡»
آية رقم 90
ﯻﯼﯽﯾ
ﯿ
(ሰዎችን ለማገድ የመካን በሮች) በተከፋፈሉት ላይ እንደ አወረድነው (በኾነ ቅጣት አሰፈራሪያችሁ ነኝ በል)፡፡
آية رقم 91
ﭑﭒﭓﭔ
ﭕ
(እነርሱም) እነዚያ ቁርኣንንን ክፍልፍሎች ያደረጉ ናቸው፡፡
آية رقم 92
ﭖﭗﭘ
ﭙ
በጌታህም እንምላለን፡፡ ሁላቸውንም እንጠይቃቸዋለን፤
آية رقم 93
ﭚﭛﭜ
ﭝ
ይሠሩት ከነበሩት ነገር ሁሉ፡፡
آية رقم 94
ﭞﭟﭠﭡﭢﭣ
ﭤ
የታዘዝክበትንም ነገር በይፋ ግለጽ፡፡ አጋሪዎችንም ተዋቸው፡፡
آية رقم 95
ﭥﭦﭧ
ﭨ
ተሳላቂዎችን ሁሉ እኛ በቅተንሃል፡፡
آية رقم 96
(እነሱም) እነዚያ ከአላህ ጋር ሌላ አምላክን ያደረጉ ናቸው፡፡ በእርግጥም (ፍጻሜያቸውን) ወደፊት ያውቃሉ፡፡
آية رقم 97
አንተም በሚሉት ነገር ልብህ የሚጠብ መኾኑን በእርግጥ እናውቃለን፡፡
آية رقم 98
ﭻﭼﭽﭾﭿﮀ
ﮁ
ጌታህንም ከማመስገን ጋር አጥራው ከሰጋጆቹም ኹን፡፡
آية رقم 99
ﮂﮃﮄﮅﮆ
ﮇ
እውነቱም (ሞት) እስኪመጣህ ድረስ ጌታህን ተገዛ፡፡
تقدم القراءة