سورة الشعراء

الترجمة الأمهرية

ترجمة معاني سورة الشعراء باللغة الأمهرية من كتاب الترجمة الأمهرية

محمد صادق

الترجمة الأمهرية

محمد صادق

آية رقم 1
ጠ.ሰ.መ. (ጧ ሲን ሚም)፡፡
آية رقم 2
ይህች ግልጽ ከኾነው መጽሐፍ አንቀጾች ናት፡፡
آية رقم 3
አማኞች ባለመኾናቸው፤ (በቁጭት) ነፍስህን ገዳይ መኾን ይፈራልሃል፡፡
ብንሻ በእነሱ ላይ ከሰማይ ተዓምረን እናወርድና አንገቶቻቸው (መሪዎቻቸው) ለእርሷ ተዋራጆች ይኾናሉ፡፡
ከአልረሕማንም ዘንድ ኣዲስ የተወረደ ቁርኣን አይመጣላቸውም፤ ከእርሱ የሚሸሹ ቢኾኑ እንጂ፡፡
آية رقم 6
በእርግጥም አስተባበሉ፡፡ የዚያም በእርሱ ይሳለቁበት የነበሩት ወሬዎች (ፍጻሜ) ይመጣባቸዋል፡፡
በዚህ አስደናቂ ምልክት አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም አማኞች አልነበሩም፡፡
آية رقم 9
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊ አዛኝ ነው፡፡
آية رقم 10
ጌታህም ሙሳን «ወደ በደለኞቹ ሕዝቦች ኺድ» በማለት በጠራው ጊዜ (አስታውስ)፡፡
آية رقم 11
«ወደ ፈርዖን ሕዝቦች (ኺድ) አላህን አይፈሩምን» (አለው)፡፡
آية رقم 12
(ሙሳም) አለ «ጌታዬ ሆይ! እኔ ሊያስተባብሉኝ እፈራለሁ፡፡
آية رقم 13
«ልቤም ይጠብባል፡፡ ምላሴም አይፈታም፡፡ ስለዚህ ወደ ሃሩን ላክ፡፡
آية رقم 14
«ለእነርሱም በእኔ ላይ (የደም) ወንጀል አልለ፡፡ ስለዚህ እንዳይገድሉኝ እፈራለሁ፡፡»
(አላህ) አለ «ተው! (አይነኩህም)፡፡ በተዓምራቶቻችንም ኺዱ፡፡ እኛ ከእናንተ ጋር ሰሚዎች ነንና፡፡
آية رقم 16
«ወደ ፈርዖንም ኺዱ፡፡ በሉትም፡- እኛ የዓለማት ጌታ መልክተኞች ነን፡፡
آية رقم 17
«የእስራኤልን ልጆች ከእኛ ጋር ልቀቅ፡፡»
(ፈርዖንም) አለ «ልጅ ኾነህ በእኛ ውስጥ አላሳደግንህምን በእኛ ውስጥም ከዕድሜህ ብዙ ዓመታትን አልተቀመጥክምን
آية رقم 19
«ያችንም የሠራሃትን ሥራህን አልሠራህምን አንተም ከውለታ ቢሶቹ ነህ» (አለ)፡፡
آية رقم 20
(ሙሳም) አለ «ያን ጊዜ እኔም ከተሳሳቱት ኾኜ ሠራኋት፡፡
«በፈራኋችሁም ጊዜ ከእንናተ ሸሸሁ፡፡ ጌታየም ለእኔ ጥበብን ሰጠኝ፡፡ ከመልክተኞቹም አደረገኝ፡፡
آية رقم 22
«ይህችም የእስራኤልን ልጆች ባሪያ በማድረግህ በእኔ ላይ የምትመጻደቅባት ጸጋ ነት፡፡»
آية رقم 23
ፈርዖን አለ «(ላከኝ የምትለው) የዓለማትም ጌታ ምንድነው»
(ሙሳ) «የሰማያትና የምድር በመካከላቸውም ያለው ሁሉ ጌታ ነው፡፡ የምታረጋግጡ ብትኾኑ (ነገሩ ይህ ነው)፤» አለው፡፡
آية رقم 25
(ፈርዖንም) በዙሪያው ላሉት ሰዎች «አትሰሙምን» አለ፡፡
آية رقم 26
(ሙሳ) «ጌታችሁና የመጀመሪያዎቹ አባቶቻችሁም ጌታ ነው» አለው፡፡
(ሙሳ) «የምሥራቅና የምዕራብ በመካከላቸውም ያለው ነገር ሁሉ ጌታ ነው፡፡ ታውቁ እንደኾናችሁ (እመኑበት)» አለው፡፡
آية رقم 29
(ፈርዖን) «ከእኔ ሌላ አምላክን ብትይዝ በውነቱ ከእስረኞቹ አደርግሃለሁ» አለ፡፡
آية رقم 30
(ሙሳ) «በግልጽ አስረጅ ብመጣህም እንኳ» አለው፡፡
آية رقم 31
«እንግዲያውስ ከእውነተኞች እንደኾንክ (አስረጁን) አምጣው» አለ፡፡
آية رقم 32
በትሩንም ጣለ፡፡ እርሷም ወዲያውኑ ግልጽ እባብ ኾነች፡፡
آية رقم 33
እጁንም አወጣ፡፡ ወዲያውም እርሷ ለተመልካቾች (የምታበራ) ነጭ ኾነች፡፡
آية رقم 34
(ፈርዖን) በዙሪያው ላሉት መማክርት «ይህ በእርግጥ ዐዋቂ ድግምተኛ ነው» አለ፡፡
آية رقم 35
«ከምድራችሁ በድግምቱ ሊያወጣችሁ ይፈልጋልና ምንን ታዛላችሁ» (አላቸው)፡፡
آية رقم 36
አሉት «እርሱን ወንድሙንም አቆይና በየከተሞቹ ሰብሳቢዎችን ላክ፡፡
آية رقم 37
«በጣም ዐዋቂ ድግምተኞችን ሁሉ ያመጡልሃልና፡፡»
آية رقم 38
ድግምተኞቹም በታወቀ ቀን ቀጠሮ ተሰበሰቡ፡፡
آية رقم 39
ለሰዎቹም «እናንተ ተሰብስባችኋልን» ተባለ፡፡
آية رقم 40
«ድግምተኞቹን እነሱ አሸናፊዎች ቢኾኑ እንከተል ዘንድ» (ተባለ)፡፡
«ድግምተኞቹም በመጡ ጊዜ ለፈርዖን እኛ አሸናፊዎች ብንሆን ለእኛ በእርግጥ ዋጋ አለን» አሉት፡፡
آية رقم 42
«አዎን፤ እናንተም ያን ጊዜ ከባለሟሎቹ ትኾናላችሁ» አላቸው፡፡
آية رقم 43
ሙሳ «ለእነርሱ እናንተ የምትጥሉትን ጣሉ» አላቸው፡፡
ገመዶቻቸውንና በትሮቻቸውንም ጣሉ፡፡ «በፈርዖንም ክብር ይኹንብን፡፡ እኛ በእርግጥ አሸናፊዎቹ እኛ ነን» አሉ፡፡
آية رقم 45
ሙሳም በትሩን ጣለ፡፡ ወዲያውም እርሷ የሚያስመስሉትን ሁሉ ትውጣለች፡፡
آية رقم 46
ድግምተኞቹም ሰጋጆች ኾነው ወደቁ፡፡
آية رقم 47
(እነሱም) አሉ «በዓለማት ጌታ አመንን፡፡
آية رقم 48
«በሙሳና በሃሩን ጌታ፡፡»
(ፈርዖንም) «ለእናንተ ሳልፈቅድላችሁ በፊት ለእርሱ አመናችሁን እርሱ ያ ድግምትን ያስተማራችሁ ታላቃችሁ ነው፡፡ ወደፊትም (የሚያገኛችሁን) በእርግጥ ታውቃላችሁ፡፡ እጆቻችሁንና እግሮቻችሁን (ቀኝና ግራን) በማናጋት እቆረርጣለሁ፡፡ ሁላችሁንም እሰቅላችኋለሁም» አለ፡፡
آية رقم 50
(እነርሱም) አሉ «ጉዳት የለብንም፡፡ እኛ ወደ ጌታችን ተመላሾች ነን፡፡
«እኛ የምእምናን መጀመሪያ በመኾናችን ጌታችን ኀጢአቶቻችንን ለእኛ ሊምር እንከጅላለን፡፡»
ወደ ሙሳም «ባሮቼን ይዘህ ሌሊት ኺድ፡፡ እናንተ የሚከተሉዋችሁ ናችሁና» ስንል ላክን፡፡
آية رقم 53
ፈርዖንም በየከተሞቹ ሰብሳቢዎችን (እንዲህ ሲል) ላከ፡፡
آية رقم 54
«እነዚህ ጥቂቶች ጭፈሮች ናቸው፡፡
آية رقم 55
«እነርሱም ለእኛ አስቆጪዎች ናቸው፡፡
آية رقم 56
«እኛም ብዙዎች ጥንቁቆች ነን፤» (አለ)፡፡
آية رقم 57
አወጣናቸውም፡፡ ከአትክልቶችና ከምንጮች፡፡
آية رقم 58
ከድልቦችም ከመልካም መቀመጫዎችም፡፡
آية رقم 59
እንደዚሁ ለእስራኤል ልጆች አወረስናትም፡፡
آية رقم 60
ፀሐይዋ ስትወጣም ተከተሉዋቸው፡፡
آية رقم 61
ሁለቱ ጭፍሮችም በተያዩ ጊዜ የሙሳ ጓዶች «እኛ(የፈርዖን ሰዎች) የሚደርሱብን ነን» አሉ፡፡
آية رقم 62
(ሙሳ) «ተዉዉ! ጌታዬ ከእኔ ጋር ነው፡፡ በእርግጥ ይመራኛል» አለ፡፡
ወደ ሙሳም «ባሕሩን በበትርህ ምታው» ስንል ላክንበት፡፡ (መታውና) ተከፈለም፡፡ ክፍሉም ሁሉ እንደ ታላቅ ጋራ ኾነ፡፡
آية رقم 64
እዚያም ዘንድ ሌሎችን አቀረብን፡፡
آية رقم 65
ሙሳንም ከእርሱ ገር ያሉትንም ሰዎች ሁሉንም አዳን፡፡
آية رقم 66
ከዚያም ሌሎቹን አሰጠምን፡፡
በዚህ ውስጥ ታላቅ ታምር አለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም አማኞች አልነበሩም፡፡
آية رقم 69
በእነሱም (በሕዝቦችህ) ላይ የኢብራሂምን ወሬ አንብብላቸው፡፡
آية رقم 70
ለአባቱና ለሕዝቦቹ «ምንን ትግገዛላችሁ» ባለ ጊዜ፡፡
آية رقم 71
«ጣዖታትን እንገዛለን፤ እርሷንም በመገዛት ላይ እንቆያለን» አሉ፡፡
آية رقم 72
(እርሱም) አለ «በጠራችኋቸው ጊዜ ይሰሟችኋልን
آية رقم 73
«ወይስ ይጠቅሟችኋልን ወይስ ይጎዷችኋልን»
آية رقم 74
«የለም! አባቶቻችን እንደዚሁ ሲሠሩ አገኘን» አሉት፡፡
آية رقم 75
«ትግገዙት የነበራችሁትን አስተዋላችሁን
آية رقم 76
«እናንተም የቀድሞዎቹ አባቶቻችሁም (የተግገዛችሁትን)፡፡»
آية رقم 77
«እነሱም (ጣዖቶቹ) ለእኔ ጠላቶች ናቸው፡፡ ግን የዓለማት ጌታ ሲቀር (እርሱ ወዳጄ ነው)፡፡
آية رقم 78
«(እርሱ) ያ የፈጠረኝ ነው፡፡ እርሱም ይመራኛል፡፡
آية رقم 79
«ያም እርሱ የሚያበላኝና የሚያጠጣኝ ነው፡፡
آية رقم 80
«በታመምኩም ጊዜ እርሱ ያሽረኛል፡፡
آية رقم 81
«ያም የሚገድለኝ ከዚያም ሕያው የሚያደርገኝ ነው፡፡
آية رقم 83
ጌታዬ ሆይ! ዕውቀትን ስጠኝ! በደጋጎቹም ሰዎች አስጠጋኝ፡፡
آية رقم 84
በኋለኞቹም ሕዝቦች ውስጥ ለእኔ መልካም ዝናን አድርግልኝ፡፡
آية رقم 85
የጸጋይቱን ገነት ከሚወርሱትም አድርገኝ፡፡
آية رقم 86
ለአባቴም ማር፡፡ እርሱ ከተሳሳቱት ነበረና፡፡
آية رقم 87
በሚቀሰቀሱበት ቀንም አታዋርደኝ፡፡
آية رقم 89
ወደ አላህ በንጹህ ልብ የመጣ ሰው ቢኾን እንጅ፡፡»
آية رقم 90
ገነትም ለፈሪዎች በምትቀረብበት (ቀን)፡፡
آية رقم 91
ገሀነምም ለጠመሞች በምትገለጽበት (ቀን)፡፡
آية رقم 92
ለእነሱም በሚባል ቀን «ትግገዟቸው የነበራችሁት የት ናቸው»
آية رقم 93
«ከአላህ ሌላ ሲኾኑ ይረዱዋችኋልን ወይስ (ለራሳቸው) ይርረዳሉን»
آية رقم 94
በውስጧም እነሱና ጠማሞቹ በፊቶቻቸው ተጥለው ይንከባለላሉ፡፡
آية رقم 95
የሰይጣንም ሰራዊቶች መላውም (ይጣላሉ)፡፡
آية رقم 96
እነርሱም በእርሷ ውስጥ የሚከራከሩ ኾነው ይላሉ፡-
آية رقم 97
በአላህ እንምላለን፤ እኛ በግልጽ መሳሳት ውስጥ ነበርን፡፡
آية رقم 98
(ጣዖቶቹን) በዓለማት ጌታ ባስተካከልናችሁ ጊዜ፡፡
آية رقم 99
አመጸኞቹም እንጅ ሌላ አላሳሳተንም፡፡
آية رقم 100
ከአማላጆችም ለእኛ ምንም የለንም፡፡
آية رقم 101
አዛኝ ወዳጂም (የለንም)፡፡
آية رقم 102
ለእኛም አንዲት ጊዜ መመለስ በኖረችንና ከአማኞቹ በኾን እንመኛለን (ይላሉ)፡፡
آية رقم 103
በዚህ ውስጥ አስደናቂ ግሳጼ አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም አማኞች አልነበሩም፡፡
آية رقم 104
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
آية رقم 105
የኑሕ ሕዝቦች መልክተኞችን አስተባበሉ፡፡
آية رقم 106
ወንድማቸው ኑሕ ለእነሱ ባላቸው ጊዜ «አትጠነቀቁምን
آية رقم 107
«እኔ ለእናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡
آية رقم 108
«አላህንም ፍሩ ታዘዙኝም፡፡
«በእርሱም ላይ ምንም ዋጋ አልጠይቃችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡
آية رقم 110
«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡»
آية رقم 111
(እነርሱም) «ወራዶቹ የተከተሉህ ኾነህ ለአንተ እናምናለን» አሉት፡፡
آية رقم 112
(እርሱም) አላቸው «ይሠሩት በነበሩት ነገር ምን ዕውቀት አለኝ፡፡
آية رقم 113
«ምርመራቸው በጌታዬ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡ ብታውቁ ኖሮ (ይህንን ትርረዱ ነበር)፡፡
آية رقم 114
«እኔም አማኞችን አባራሪ አይደለሁም፡፡
آية رقم 115
«እኔ ግልጽ አስፈራሪ እንጅ ሌላ አይደለሁም፡፡»
آية رقم 116
«ኑሕ ሆይ! (ከምትለው) ባትከለከል በእርግጥ ከሚወገሩት ትኾናለህ» አሉት፡፡
آية رقم 117
(እርሱም) አለ «ጌታዬ ሆይ! ሕዝቦቼ አስተባበሉኝ፡፡
آية رقم 118
«በእኔና በእነርሱም መካከል (ተገቢ) ፍርድን ፍረድ፡፡ አድነኝም፡፡ ከእኔ ጋር ያሉትንም ምእምናን፡፡»
آية رقم 119
እርሱንም ከእርሱ ጋር ያለውንም ሁሉ በተመላው መርከብ ውስጥ አዳን፡፡
آية رقم 120
ከዚያም በኋላ ቀሪዎቹን አሰጠምን፡፡
آية رقم 121
በዚህ ውስጥ ታላቅ ግሳጼ አለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም አማኞች አልነበሩም፡፡
آية رقم 122
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
آية رقم 123
ዓድ መልክተኞችን አስተባበለች፡፡
آية رقم 124
ወንድማቸው ሁድ ለነርሱ ባላቸው ጊዜ «አትጠነቀቁምን
آية رقم 125
«እኔ ለናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡
آية رقم 126
«አላህንም ፍሩ ታዘዙኝም፡፡
«በእርሱም ላይ ምንም ዋጋ አለምናችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡
آية رقم 128
«የምትጫወቱ ኾናችሁ በከፍተኛ ስፍራ ሁሉ ላይ ምልክትን ትገነባላችሁን
آية رقم 129
«የውሃ ማጠራቀሚያዎችንና ሕንፃዎችንም ዘላለም መኖርን የምትከጅሉ ኾናችሁ ትሠራላችሁን
آية رقم 130
«በቀጣችሁም ጊዜ ጨካኞች ኾናችሁ ትቀጣላችሁን
آية رقم 131
«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡
آية رقم 132
«ያንንም በምታውቁት (ጸጋ) ያጣቀማችሁን ፍሩ፡፡
آية رقم 133
«በእንስሳዎችና በልጆች ያጣቀማችሁን፡፡
آية رقم 134
«በአትክልቶችና በምንጮችም፡፡
آية رقم 135
«እኔ በእናንተ ላይ የታላቅን ቀን ቅጣት እፈራለሁና፡፡»
آية رقم 136
(እነርሱም) አሉ «ብትገስጽም ወይም ከገሳጮቹ ባትኾንም በእኛ ላይ እኩል ነው፤ (ያለንበትን አንለቅም)፡፡
آية رقم 137
«ይህ የፊተኞቹ ሰዎች ፀባይ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡
آية رقم 138
«እኛም የምንቅቀጣ አይደለንም» (አሉ)፡፡
አስተባበሉትም፡፡ አጠፋናቸውም፡፡ በዚህም ውስጥ እርግጠኛ ግሳጼ አለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም ምእመናን አልነበሩም፡፡
آية رقم 140
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
آية رقم 141
ሰሙድ መልክተኞችን አስተባበለች፡፡
آية رقم 142
ወንድማቸው ሷሊህ ለእነርሱ ባላቸው ጊዜ «አትጠነቀቁምን
آية رقم 143
«እኔ ለእናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡
آية رقم 144
«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡
«በእርሱም ላይ ምንም ዋጋ አልለምናችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡
آية رقم 146
«በዚያ እዚህ ባለው (ጸጋ) ውስጥ የረካችሁ ኾናችሁ ትተዋላችሁን
آية رقم 147
«በአትክልቶችና በምንጮች ውስጥ፡፡
آية رقم 148
«በአዝመራዎችም ፍሬዋ የበሰለ በኾነች ዘንባባም፤ (ውስጥ ትተዋላችሁን)
آية رقم 149
«ብልሆች ኾናችሁ ከጋራዎች ቤቶችንም ትጠርባላችሁ፡፡
آية رقم 150
«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡
آية رقم 151
«የወሰን አላፊዎችንም ትዕዛዝ አትከተሉ፡፡
آية رقم 152
«የእነዚያን በምድር ላይ የሚያጠፉትንና የማያበጁትን፡፡»
آية رقم 153
(እነሱም) አሉ «አንተ በብዙ ከተደገመባቸው ሰዎች ብቻ ነህ፡፡
«አንተ ብጤያችን ሰው እንጅ ሌላ አይደለህም፡፡ ከእውነተኞቹም እንደኾንክ ተዓምርን አምጣ፡፡»
آية رقم 155
(እርሱም) አለ «ይህች ግመል ናት፡፡ ለእርሷ የመጠጥ ፋንታ አላት፡፡ ለእናንተም የታወቀ ቀን ፋንታ አላችሁ፡፡
آية رقم 156
«በክፉም አትንኳት፡፡ የታላቅ ቀን ቅጣት ይይዛችኋልና፡፡»
آية رقم 157
ወጓትም፡፡ ወዲያውም ተጸጻቾች ኾነው አነጉ፡፡
ቅጣቱም ያዛቸው፡፡ በዚህም ውስጥ ግሳፄ አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም ምእመናን አልነበሩም፡፡
آية رقم 159
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
آية رقم 160
የሉጥ ሕዝቦች መልክተኞችን አስተባባሉ፡፡
آية رقم 162
«እኔ ለእናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡
آية رقم 163
«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡
«በእርሱም ላይ ምንም ዋጋ አልለምናችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡
آية رقم 165
«ከዓለማት ሰዎች ወንዶችን ትመጣላችሁን
«ከሚስቶቻችሁም ጌታችሁ ለናንተ የፈጠረላችሁን ትተዋላችሁን በእውነቱ እናንተ ወሰን አላፊዎች ሕዝቦ ናችሁ፡፡»
آية رقم 167
(እነርሱም) አሉ «ሉጥ ሆይ! ባትከለከል በእርግጥ (ከአገር) ከሚወጡት ትኾናለህ፡፡»
آية رقم 168
(እርሱም) አለ «እኔ ሥራችሁን ከሚጠሉት ሰዎች ነኝ፡፡
آية رقم 169
«ጌታዬ ሆይ! እኔንም ቤተሰቦቼንም ከሚሠሩት ሥራ (ቅጣት) አድነን፡፡»
آية رقم 170
እርሱንም ቤተሰቦቹንም በጠቅላላ አዳንናቸው፡፡
آية رقم 171
በቀሪዎቹ ውስጥ የኾነች አሮጊት ብቻ ስትቀር (እርሷ ጠፋች)፡፡
آية رقم 172
ከዚያም ሌሎቹን አጠፋን፡፡
آية رقم 173
በእነሱም ላይ (የድንጋይን) ዝናምን አዘነምንባቸው፡፡ የተስፈራሪዎቹም ዝናም (ምንኛ) ከፋ፡፡
آية رقم 174
በዚህ ውስጥ አስደናቂ ተዓምር አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም ምእመናን አልነበሩም፡፡
آية رقم 175
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
آية رقم 176
የአይከት ሰዎች መልክተኞችን አስተባበሉ፤
آية رقم 177
ሹዕይብ ለእነርሱ ባላቸው ጊዜ «አትጠነቀቁምን
آية رقم 178
«እኔ ለእናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡
آية رقم 179
«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡
«በርሱም ላይ ምንም ዋጋ አልጠይቃችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡
آية رقم 182
«በትክክለኛ ሚዛንም መዝኑ፡፡
آية رقم 183
«ሰዎችንም ነገሮቻቸውን አታጉድሉባቸው፡፡ በምድርም ላይ አጥፊዎች ኾናችሁ አታበላሹ፡፡
آية رقم 184
«ያንንም የፈጠራችሁን የቀድሞዎቹንም ፍጡሮች (የፈጠረውን) ፍሩ፡፡»
آية رقم 185
አሉ «አንተ በብዛት ከተደገመባቸው ሰዎች ነህ፡፡
آية رقم 186
«አንተም ብጤያችን ሰው እንጅ ሌላ አይደለህም፡፡ እነሆ ከውሸታሞች ነህ ብለን እንጠረጥርሃለን፡፡
آية رقم 187
«ከእውነተኞቹም እንደኾንክ በእኛ ላይ ከሰማይ ቁራጭን ጣልብን፡፡»
آية رقم 188
«ጌታዬ የምትሠሩትን ሁሉ ዐዋቂ ነው፤» አላቸው፡፡
አስተባበሉትም፡፡ የጥላይቷ ቀን ቅጣትም ያዛቸው፡፡ እርሱ የከባድ ቀን ቅጣት ነበርና፡፡
آية رقم 190
በዚህ ውስጥ አስደናቂ ተዓምር አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም ምእምናን አልነበሩም፡፡
آية رقم 191
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
آية رقم 192
እርሱም (ቁርኣን) በእርግጥ ከዓለማት ጌታ የተወረደ ነው፡፡
آية رقم 193
እርሱን ታማኙ መንፈስ (ጂብሪል) አወረደው፤
آية رقم 194
ከአስፈራሪዎቹ (ነቢያት) ትኾን ዘንድ በልብህ ላይ (አወረደው)፡፡
آية رقم 195
ግልጽ በኾነ ዐረብኛ ቋንቋ፡፡
آية رقم 196
እርሱም (ቁርኣን) በቀድሞዎቹ መጻሐፍት ውስጥ (የተወሳ ነው)፡፡
آية رقم 197
የእስራኤል ልጆች ሊቃውንት የሚያውቁት መኾኑ ለእነርሱ (ለመካ ከሓዲዎች) ምልክት አይኾናቸውምን
آية رقم 198
ከአዕጀሞች ባንዱ ላይ ባወረድነውም ኖሮ፤
آية رقم 199
በእነርሱ ላይ ባነበበውም በእርሱ አማኞች አይኾኑም ነበር፡፡
آية رقم 200
እንደዚሁ (ማስተባበልን) በተንኮለኞች ልቦች ውስጥ አስገባነው፡፡
آية رقم 201
አሳማሚ ቅጣትን እስከሚያዩ ድረስ በእርሱ አያምኑም፡፡
آية رقم 202
እነርሱ የማያውቁ ሲኾኑ (ቅጣቱ) ድንገት እስከሚመጣባቸውም ድረስ (አያምኑም)፡፡
آية رقم 203
(በመጣባቸው ጊዜ) «እኛ የምንቆይ ነን» እስከሚሉም (አያምኑም)፡፡
آية رقم 204
በቅጣታችን ያቻኩላሉን
آية رقم 205
አየህን ብዙ ዓመታትን ብናጣቅማቸው፤
آية رقم 206
ከዚያም ያ ይስፈራሩበት የነበሩት ቢመጣባቸው፤
آية رقم 207
ይጣቀሙበት የነበሩት ሁሉ ከእነሱ ምንም አያብቃቃቸውም፡፡
آية رقم 208
አንዲትንም ከተማ ለእርሷ አስፈራሪዎች ያሏት (እና ያስተባበለች) ኾና እንጅ አላጠፋንም፡፡
آية رقم 209
(ይህች) ግሳፄ ናት፡፡ በዳዮችም አልነበርንም፡፡
آية رقم 210
ሰይጣናትም እርሱን (ቁርኣንን) አላወረዱትም፡፡
آية رقم 211
ለእነርሱም አይገባቸውም፤ አይችሉምም፡፡
آية رقم 212
እነርሱ (የመላእክትን ንግግር) ከመስማት ተከለከሉ ናቸው፡፡
آية رقم 214
ቅርቦች ዘመዶችህንም አስጠንቅቅ፡፡
آية رقم 215
ከምእምናንም ለተከተሉህ ሰዎች ክንፍህን ዝቅ አድርግ፤ (ልዝብ ኹን)፡፡
آية رقم 216
«እንቢ» ቢሉህም «እኔ ከምትሠሩት ንጹሕ ነኝ» በላቸው፡፡
آية رقم 217
አሸናፊ አዛኝ በኾነው (ጌታህ) ላይም ተጠጋ፡፡
آية رقم 218
በዚያ ለሶላት በምትቆም ጊዜ በሚያይህ፡፡
آية رقم 219
በሰጋጆች ውስጥ መዘዋወርህንም (በሚያየው ጌታህ ላይ ተጠጋ)፡፡
آية رقم 220
እነሆ እርሱ ሰሚው ዐዋቂው ነውና፡፡
آية رقم 221
ሰይጣናት በማን ላይ እንደሚወርዱ ልንገራችሁን
آية رقم 222
በውሸታም ኀጢአተኛ ሁሉ ላይ ይወርዳሉ፡፡
آية رقم 223
የሰሙትን (ወደ ጠንቋዮች) ይጥላሉ፡፡ አብዛኞቻቸውም ውሸታሞች ናቸው፡፡
آية رقم 224
ባለ ቅኔዎችንም ጠማማዎቹ ይከተሉዋቸዋል፡፡
آية رقم 225
እነርሱ በ(ንግግር) ሸለቆ ሁሉ የሚዋልሉ መኾናቸውን አታይምን
آية رقم 226
እነሱም የማይሠሩትን ነገር የሚናገሩ መኾናቸውን (አታይምን)፤
እነዚያ ያመኑና መልካም ሥራዎችን የሠሩ አላህንም በብዛት ያወሱ ከተበደሉም በኋላ (በቅኔ) የተከላከሉ ሲቀሩ፤ (እነርሱ አይወቀሱም)፡፡ እነዚያም የበደሉ (ከሞቱ በኋላ) እንዴት ያለን መመለስ እንደሚመለሱ በእርግጥ ያውቃሉ፡፡
تقدم القراءة