ترجمة معاني سورة الشعراء باللغة الأمهرية من كتاب الترجمة الأمهرية
محمد صادق
آية رقم 1
ﭑ
ﭒ
ጠ.ሰ.መ. (ጧ ሲን ሚም)፡፡
آية رقم 2
ﭓﭔﭕﭖ
ﭗ
ይህች ግልጽ ከኾነው መጽሐፍ አንቀጾች ናት፡፡
آية رقم 3
ﭘﭙﭚﭛﭜﭝ
ﭞ
አማኞች ባለመኾናቸው፤ (በቁጭት) ነፍስህን ገዳይ መኾን ይፈራልሃል፡፡
آية رقم 4
ብንሻ በእነሱ ላይ ከሰማይ ተዓምረን እናወርድና አንገቶቻቸው (መሪዎቻቸው) ለእርሷ ተዋራጆች ይኾናሉ፡፡
آية رقم 5
ከአልረሕማንም ዘንድ ኣዲስ የተወረደ ቁርኣን አይመጣላቸውም፤ ከእርሱ የሚሸሹ ቢኾኑ እንጂ፡፡
آية رقم 6
በእርግጥም አስተባበሉ፡፡ የዚያም በእርሱ ይሳለቁበት የነበሩት ወሬዎች (ፍጻሜ) ይመጣባቸዋል፡፡
آية رقم 7
ወደ ምድርም በውስጧ ከመልካም (በቃይ) ጎሳ ሁሉ ብዙን እንዳበቀልን አላዩምን፡፡
آية رقم 8
በዚህ አስደናቂ ምልክት አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም አማኞች አልነበሩም፡፡
آية رقم 9
ﮖﮗﮘﮙﮚ
ﮛ
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊ አዛኝ ነው፡፡
آية رقم 10
ጌታህም ሙሳን «ወደ በደለኞቹ ሕዝቦች ኺድ» በማለት በጠራው ጊዜ (አስታውስ)፡፡
آية رقم 11
ﮥﮦﮧﮨﮩ
ﮪ
«ወደ ፈርዖን ሕዝቦች (ኺድ) አላህን አይፈሩምን» (አለው)፡፡
آية رقم 12
ﮫﮬﮭﮮﮯﮰ
ﮱ
(ሙሳም) አለ «ጌታዬ ሆይ! እኔ ሊያስተባብሉኝ እፈራለሁ፡፡
آية رقم 13
«ልቤም ይጠብባል፡፡ ምላሴም አይፈታም፡፡ ስለዚህ ወደ ሃሩን ላክ፡፡
آية رقم 14
ﯜﯝﯞﯟﯠﯡ
ﯢ
«ለእነርሱም በእኔ ላይ (የደም) ወንጀል አልለ፡፡ ስለዚህ እንዳይገድሉኝ እፈራለሁ፡፡»
آية رقم 15
(አላህ) አለ «ተው! (አይነኩህም)፡፡ በተዓምራቶቻችንም ኺዱ፡፡ እኛ ከእናንተ ጋር ሰሚዎች ነንና፡፡
آية رقم 16
«ወደ ፈርዖንም ኺዱ፡፡ በሉትም፡- እኛ የዓለማት ጌታ መልክተኞች ነን፡፡
آية رقم 17
ﯵﯶﯷﯸﯹ
ﯺ
«የእስራኤልን ልጆች ከእኛ ጋር ልቀቅ፡፡»
آية رقم 18
(ፈርዖንም) አለ «ልጅ ኾነህ በእኛ ውስጥ አላሳደግንህምን በእኛ ውስጥም ከዕድሜህ ብዙ ዓመታትን አልተቀመጥክምን
آية رقم 19
«ያችንም የሠራሃትን ሥራህን አልሠራህምን አንተም ከውለታ ቢሶቹ ነህ» (አለ)፡፡
آية رقم 20
ﭑﭒﭓﭔﭕﭖ
ﭗ
(ሙሳም) አለ «ያን ጊዜ እኔም ከተሳሳቱት ኾኜ ሠራኋት፡፡
آية رقم 21
«በፈራኋችሁም ጊዜ ከእንናተ ሸሸሁ፡፡ ጌታየም ለእኔ ጥበብን ሰጠኝ፡፡ ከመልክተኞቹም አደረገኝ፡፡
آية رقم 22
«ይህችም የእስራኤልን ልጆች ባሪያ በማድረግህ በእኔ ላይ የምትመጻደቅባት ጸጋ ነት፡፡»
آية رقم 23
ﭭﭮﭯﭰﭱ
ﭲ
ፈርዖን አለ «(ላከኝ የምትለው) የዓለማትም ጌታ ምንድነው»
آية رقم 24
(ሙሳ) «የሰማያትና የምድር በመካከላቸውም ያለው ሁሉ ጌታ ነው፡፡ የምታረጋግጡ ብትኾኑ (ነገሩ ይህ ነው)፤» አለው፡፡
آية رقم 25
ﭾﭿﮀﮁﮂ
ﮃ
(ፈርዖንም) በዙሪያው ላሉት ሰዎች «አትሰሙምን» አለ፡፡
آية رقم 26
ﮄﮅﮆﮇﮈ
ﮉ
(ሙሳ) «ጌታችሁና የመጀመሪያዎቹ አባቶቻችሁም ጌታ ነው» አለው፡፡
آية رقم 27
(ፈርዖን)
آية رقم 28
(ሙሳ) «የምሥራቅና የምዕራብ በመካከላቸውም ያለው ነገር ሁሉ ጌታ ነው፡፡ ታውቁ እንደኾናችሁ (እመኑበት)» አለው፡፡
آية رقم 29
(ፈርዖን) «ከእኔ ሌላ አምላክን ብትይዝ በውነቱ ከእስረኞቹ አደርግሃለሁ» አለ፡፡
آية رقم 30
ﮦﮧﮨﮩﮪ
ﮫ
(ሙሳ) «በግልጽ አስረጅ ብመጣህም እንኳ» አለው፡፡
آية رقم 31
«እንግዲያውስ ከእውነተኞች እንደኾንክ (አስረጁን) አምጣው» አለ፡፡
آية رقم 32
ﯕﯖﯗﯘﯙﯚ
ﯛ
በትሩንም ጣለ፡፡ እርሷም ወዲያውኑ ግልጽ እባብ ኾነች፡፡
آية رقم 33
ﯜﯝﯞﯟﯠﯡ
ﯢ
እጁንም አወጣ፡፡ ወዲያውም እርሷ ለተመልካቾች (የምታበራ) ነጭ ኾነች፡፡
آية رقم 34
(ፈርዖን) በዙሪያው ላሉት መማክርት «ይህ በእርግጥ ዐዋቂ ድግምተኛ ነው» አለ፡፡
آية رقم 35
«ከምድራችሁ በድግምቱ ሊያወጣችሁ ይፈልጋልና ምንን ታዛላችሁ» (አላቸው)፡፡
آية رقم 36
አሉት «እርሱን ወንድሙንም አቆይና በየከተሞቹ ሰብሳቢዎችን ላክ፡፡
آية رقم 37
ﯼﯽﯾﯿ
ﰀ
«በጣም ዐዋቂ ድግምተኞችን ሁሉ ያመጡልሃልና፡፡»
آية رقم 38
ﰁﰂﰃﰄﰅ
ﰆ
ድግምተኞቹም በታወቀ ቀን ቀጠሮ ተሰበሰቡ፡፡
آية رقم 39
ﰇﰈﰉﰊﰋ
ﰌ
ለሰዎቹም «እናንተ ተሰብስባችኋልን» ተባለ፡፡
آية رقم 40
«ድግምተኞቹን እነሱ አሸናፊዎች ቢኾኑ እንከተል ዘንድ» (ተባለ)፡፡
آية رقم 41
«ድግምተኞቹም በመጡ ጊዜ ለፈርዖን እኛ አሸናፊዎች ብንሆን ለእኛ በእርግጥ ዋጋ አለን» አሉት፡፡
آية رقم 42
ﭦﭧﭨﭩﭪﭫ
ﭬ
«አዎን፤ እናንተም ያን ጊዜ ከባለሟሎቹ ትኾናላችሁ» አላቸው፡፡
آية رقم 43
ሙሳ «ለእነርሱ እናንተ የምትጥሉትን ጣሉ» አላቸው፡፡
آية رقم 44
ገመዶቻቸውንና በትሮቻቸውንም ጣሉ፡፡ «በፈርዖንም ክብር ይኹንብን፡፡ እኛ በእርግጥ አሸናፊዎቹ እኛ ነን» አሉ፡፡
آية رقم 45
ሙሳም በትሩን ጣለ፡፡ ወዲያውም እርሷ የሚያስመስሉትን ሁሉ ትውጣለች፡፡
آية رقم 46
ﮈﮉﮊ
ﮋ
ድግምተኞቹም ሰጋጆች ኾነው ወደቁ፡፡
آية رقم 47
ﮌﮍﮎﮏ
ﮐ
(እነሱም) አሉ «በዓለማት ጌታ አመንን፡፡
آية رقم 48
ﮑﮒﮓ
ﮔ
«በሙሳና በሃሩን ጌታ፡፡»
آية رقم 49
(ፈርዖንም) «ለእናንተ ሳልፈቅድላችሁ በፊት ለእርሱ አመናችሁን እርሱ ያ ድግምትን ያስተማራችሁ ታላቃችሁ ነው፡፡ ወደፊትም (የሚያገኛችሁን) በእርግጥ ታውቃላችሁ፡፡ እጆቻችሁንና እግሮቻችሁን (ቀኝና ግራን) በማናጋት እቆረርጣለሁ፡፡ ሁላችሁንም እሰቅላችኋለሁም» አለ፡፡
آية رقم 50
(እነርሱም) አሉ «ጉዳት የለብንም፡፡ እኛ ወደ ጌታችን ተመላሾች ነን፡፡
آية رقم 51
«እኛ የምእምናን መጀመሪያ በመኾናችን ጌታችን ኀጢአቶቻችንን ለእኛ ሊምር እንከጅላለን፡፡»
آية رقم 52
ወደ ሙሳም «ባሮቼን ይዘህ ሌሊት ኺድ፡፡ እናንተ የሚከተሉዋችሁ ናችሁና» ስንል ላክን፡፡
آية رقم 53
ﯭﯮﯯﯰﯱ
ﯲ
ፈርዖንም በየከተሞቹ ሰብሳቢዎችን (እንዲህ ሲል) ላከ፡፡
آية رقم 54
ﯳﯴﯵﯶ
ﯷ
«እነዚህ ጥቂቶች ጭፈሮች ናቸው፡፡
آية رقم 55
ﯸﯹﯺ
ﯻ
«እነርሱም ለእኛ አስቆጪዎች ናቸው፡፡
آية رقم 56
ﯼﯽﯾ
ﯿ
«እኛም ብዙዎች ጥንቁቆች ነን፤» (አለ)፡፡
آية رقم 57
ﰀﰁﰂﰃ
ﰄ
አወጣናቸውም፡፡ ከአትክልቶችና ከምንጮች፡፡
آية رقم 58
ﰅﰆﰇ
ﰈ
ከድልቦችም ከመልካም መቀመጫዎችም፡፡
آية رقم 59
ﰉﰊﰋﰌﰍ
ﰎ
እንደዚሁ ለእስራኤል ልጆች አወረስናትም፡፡
آية رقم 60
ﰏﰐ
ﰑ
ፀሐይዋ ስትወጣም ተከተሉዋቸው፡፡
آية رقم 61
ሁለቱ ጭፍሮችም በተያዩ ጊዜ የሙሳ ጓዶች «እኛ(የፈርዖን ሰዎች) የሚደርሱብን ነን» አሉ፡፡
آية رقم 62
(ሙሳ) «ተዉዉ! ጌታዬ ከእኔ ጋር ነው፡፡ በእርግጥ ይመራኛል» አለ፡፡
آية رقم 63
ወደ ሙሳም «ባሕሩን በበትርህ ምታው» ስንል ላክንበት፡፡ (መታውና) ተከፈለም፡፡ ክፍሉም ሁሉ እንደ ታላቅ ጋራ ኾነ፡፡
آية رقم 64
ﭱﭲﭳ
ﭴ
እዚያም ዘንድ ሌሎችን አቀረብን፡፡
آية رقم 65
ﭵﭶﭷﭸﭹ
ﭺ
ሙሳንም ከእርሱ ገር ያሉትንም ሰዎች ሁሉንም አዳን፡፡
آية رقم 66
ﭻﭼﭽ
ﭾ
ከዚያም ሌሎቹን አሰጠምን፡፡
آية رقم 67
በዚህ ውስጥ ታላቅ ታምር አለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም አማኞች አልነበሩም፡፡
آية رقم 68
ﮉﮊﮋﮌﮍ
ﮎ
ጌታህም እርሱ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
آية رقم 69
ﮏﮐﮑﮒ
ﮓ
በእነሱም (በሕዝቦችህ) ላይ የኢብራሂምን ወሬ አንብብላቸው፡፡
آية رقم 70
ﮔﮕﮖﮗﮘﮙ
ﮚ
ለአባቱና ለሕዝቦቹ «ምንን ትግገዛላችሁ» ባለ ጊዜ፡፡
آية رقم 71
ﮛﮜﮝﮞﮟﮠ
ﮡ
«ጣዖታትን እንገዛለን፤ እርሷንም በመገዛት ላይ እንቆያለን» አሉ፡፡
آية رقم 72
ﮢﮣﮤﮥﮦ
ﮧ
(እርሱም) አለ «በጠራችኋቸው ጊዜ ይሰሟችኋልን
آية رقم 73
ﮨﮩﮪﮫ
ﮬ
«ወይስ ይጠቅሟችኋልን ወይስ ይጎዷችኋልን»
آية رقم 74
ﮭﮮﮯﮰﮱﯓ
ﯔ
«የለም! አባቶቻችን እንደዚሁ ሲሠሩ አገኘን» አሉት፡፡
آية رقم 75
ﯕﯖﯗﯘﯙ
ﯚ
«ትግገዙት የነበራችሁትን አስተዋላችሁን
آية رقم 76
ﯛﯜﯝ
ﯞ
«እናንተም የቀድሞዎቹ አባቶቻችሁም (የተግገዛችሁትን)፡፡»
آية رقم 77
ﯟﯠﯡﯢﯣﯤ
ﯥ
«እነሱም (ጣዖቶቹ) ለእኔ ጠላቶች ናቸው፡፡ ግን የዓለማት ጌታ ሲቀር (እርሱ ወዳጄ ነው)፡፡
آية رقم 78
ﯦﯧﯨﯩ
ﯪ
«(እርሱ) ያ የፈጠረኝ ነው፡፡ እርሱም ይመራኛል፡፡
آية رقم 79
ﯫﯬﯭﯮ
ﯯ
«ያም እርሱ የሚያበላኝና የሚያጠጣኝ ነው፡፡
آية رقم 80
ﯰﯱﯲﯳ
ﯴ
«በታመምኩም ጊዜ እርሱ ያሽረኛል፡፡
آية رقم 81
ﯵﯶﯷﯸ
ﯹ
«ያም የሚገድለኝ ከዚያም ሕያው የሚያደርገኝ ነው፡፡
آية رقم 82
ያም በፍርዱ ቀን ኀጢአቴን ለእኔ ሊምር የምከጅለው ነው፡፡
آية رقم 83
ﰃﰄﰅﰆﰇﰈ
ﰉ
ጌታዬ ሆይ! ዕውቀትን ስጠኝ! በደጋጎቹም ሰዎች አስጠጋኝ፡፡
آية رقم 84
ﭑﭒﭓﭔﭕﭖ
ﭗ
በኋለኞቹም ሕዝቦች ውስጥ ለእኔ መልካም ዝናን አድርግልኝ፡፡
آية رقم 85
ﭘﭙﭚﭛﭜ
ﭝ
የጸጋይቱን ገነት ከሚወርሱትም አድርገኝ፡፡
آية رقم 86
ﭞﭟﭠﭡﭢﭣ
ﭤ
ለአባቴም ማር፡፡ እርሱ ከተሳሳቱት ነበረና፡፡
آية رقم 87
ﭥﭦﭧﭨ
ﭩ
በሚቀሰቀሱበት ቀንም አታዋርደኝ፡፡
آية رقم 88
ﭪﭫﭬﭭﭮﭯ
ﭰ
ገንዘብም ልጆችም በማይጠቅሙበት ቀን፡፡
آية رقم 89
ﭱﭲﭳﭴﭵﭶ
ﭷ
ወደ አላህ በንጹህ ልብ የመጣ ሰው ቢኾን እንጅ፡፡»
آية رقم 90
ﭸﭹﭺ
ﭻ
ገነትም ለፈሪዎች በምትቀረብበት (ቀን)፡፡
آية رقم 91
ﭼﭽﭾ
ﭿ
ገሀነምም ለጠመሞች በምትገለጽበት (ቀን)፡፡
آية رقم 92
ﮀﮁﮂﮃﮄﮅ
ﮆ
ለእነሱም በሚባል ቀን «ትግገዟቸው የነበራችሁት የት ናቸው»
آية رقم 93
«ከአላህ ሌላ ሲኾኑ ይረዱዋችኋልን ወይስ (ለራሳቸው) ይርረዳሉን»
آية رقم 94
ﮏﮐﮑﮒ
ﮓ
በውስጧም እነሱና ጠማሞቹ በፊቶቻቸው ተጥለው ይንከባለላሉ፡፡
آية رقم 95
ﮔﮕﮖ
ﮗ
የሰይጣንም ሰራዊቶች መላውም (ይጣላሉ)፡፡
آية رقم 96
ﮘﮙﮚﮛ
ﮜ
እነርሱም በእርሷ ውስጥ የሚከራከሩ ኾነው ይላሉ፡-
آية رقم 97
ﮝﮞﮟﮠﮡﮢ
ﮣ
በአላህ እንምላለን፤ እኛ በግልጽ መሳሳት ውስጥ ነበርን፡፡
آية رقم 98
ﮤﮥﮦﮧ
ﮨ
(ጣዖቶቹን) በዓለማት ጌታ ባስተካከልናችሁ ጊዜ፡፡
آية رقم 99
ﮩﮪﮫﮬ
ﮭ
አመጸኞቹም እንጅ ሌላ አላሳሳተንም፡፡
آية رقم 100
ﮮﮯﮰﮱ
ﯓ
ከአማላጆችም ለእኛ ምንም የለንም፡፡
آية رقم 101
ﯔﯕﯖ
ﯗ
አዛኝ ወዳጂም (የለንም)፡፡
آية رقم 102
ለእኛም አንዲት ጊዜ መመለስ በኖረችንና ከአማኞቹ በኾን እንመኛለን (ይላሉ)፡፡
آية رقم 103
በዚህ ውስጥ አስደናቂ ግሳጼ አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም አማኞች አልነበሩም፡፡
آية رقم 104
ﯪﯫﯬﯭﯮ
ﯯ
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
آية رقم 105
ﯰﯱﯲﯳ
ﯴ
የኑሕ ሕዝቦች መልክተኞችን አስተባበሉ፡፡
آية رقم 106
ወንድማቸው ኑሕ ለእነሱ ባላቸው ጊዜ «አትጠነቀቁምን
آية رقم 107
ﯽﯾﯿﰀ
ﰁ
«እኔ ለእናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡
آية رقم 108
ﰂﰃﰄ
ﰅ
«አላህንም ፍሩ ታዘዙኝም፡፡
آية رقم 109
«በእርሱም ላይ ምንም ዋጋ አልጠይቃችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡
آية رقم 110
ﰓﰔﰕ
ﰖ
«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡»
آية رقم 111
ﰗﰘﰙﰚﰛﰜ
ﰝ
(እነርሱም) «ወራዶቹ የተከተሉህ ኾነህ ለአንተ እናምናለን» አሉት፡፡
آية رقم 112
ﭑﭒﭓﭔﭕﭖ
ﭗ
(እርሱም) አላቸው «ይሠሩት በነበሩት ነገር ምን ዕውቀት አለኝ፡፡
آية رقم 113
«ምርመራቸው በጌታዬ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡ ብታውቁ ኖሮ (ይህንን ትርረዱ ነበር)፡፡
آية رقم 114
ﭡﭢﭣﭤ
ﭥ
«እኔም አማኞችን አባራሪ አይደለሁም፡፡
آية رقم 115
ﭦﭧﭨﭩﭪ
ﭫ
«እኔ ግልጽ አስፈራሪ እንጅ ሌላ አይደለሁም፡፡»
آية رقم 116
«ኑሕ ሆይ! (ከምትለው) ባትከለከል በእርግጥ ከሚወገሩት ትኾናለህ» አሉት፡፡
آية رقم 117
ﭵﭶﭷﭸﭹ
ﭺ
(እርሱም) አለ «ጌታዬ ሆይ! ሕዝቦቼ አስተባበሉኝ፡፡
آية رقم 118
«በእኔና በእነርሱም መካከል (ተገቢ) ፍርድን ፍረድ፡፡ አድነኝም፡፡ ከእኔ ጋር ያሉትንም ምእምናን፡፡»
آية رقم 119
ﮅﮆﮇﮈﮉﮊ
ﮋ
እርሱንም ከእርሱ ጋር ያለውንም ሁሉ በተመላው መርከብ ውስጥ አዳን፡፡
آية رقم 120
ﮌﮍﮎﮏ
ﮐ
ከዚያም በኋላ ቀሪዎቹን አሰጠምን፡፡
آية رقم 121
በዚህ ውስጥ ታላቅ ግሳጼ አለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም አማኞች አልነበሩም፡፡
آية رقم 122
ﮛﮜﮝﮞﮟ
ﮠ
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
آية رقم 123
ﮡﮢﮣ
ﮤ
ዓድ መልክተኞችን አስተባበለች፡፡
آية رقم 124
ወንድማቸው ሁድ ለነርሱ ባላቸው ጊዜ «አትጠነቀቁምን
آية رقم 125
ﮭﮮﮯﮰ
ﮱ
«እኔ ለናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡
آية رقم 126
ﯓﯔﯕ
ﯖ
«አላህንም ፍሩ ታዘዙኝም፡፡
آية رقم 127
«በእርሱም ላይ ምንም ዋጋ አለምናችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡
آية رقم 128
ﯤﯥﯦﯧﯨ
ﯩ
«የምትጫወቱ ኾናችሁ በከፍተኛ ስፍራ ሁሉ ላይ ምልክትን ትገነባላችሁን
آية رقم 129
ﯪﯫﯬﯭ
ﯮ
«የውሃ ማጠራቀሚያዎችንና ሕንፃዎችንም ዘላለም መኖርን የምትከጅሉ ኾናችሁ ትሠራላችሁን
آية رقم 130
ﯯﯰﯱﯲ
ﯳ
«በቀጣችሁም ጊዜ ጨካኞች ኾናችሁ ትቀጣላችሁን
آية رقم 131
ﯴﯵﯶ
ﯷ
«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡
آية رقم 132
ﯸﯹﯺﯻﯼ
ﯽ
«ያንንም በምታውቁት (ጸጋ) ያጣቀማችሁን ፍሩ፡፡
آية رقم 133
ﯾﯿﰀ
ﰁ
«በእንስሳዎችና በልጆች ያጣቀማችሁን፡፡
آية رقم 134
ﰂﰃ
ﰄ
«በአትክልቶችና በምንጮችም፡፡
آية رقم 135
ﰅﰆﰇﰈﰉﰊ
ﰋ
«እኔ በእናንተ ላይ የታላቅን ቀን ቅጣት እፈራለሁና፡፡»
آية رقم 136
(እነርሱም) አሉ «ብትገስጽም ወይም ከገሳጮቹ ባትኾንም በእኛ ላይ እኩል ነው፤ (ያለንበትን አንለቅም)፡፡
آية رقم 137
ﭑﭒﭓﭔﭕ
ﭖ
«ይህ የፊተኞቹ ሰዎች ፀባይ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡
آية رقم 138
ﭗﭘﭙ
ﭚ
«እኛም የምንቅቀጣ አይደለንም» (አሉ)፡፡
آية رقم 139
አስተባበሉትም፡፡ አጠፋናቸውም፡፡ በዚህም ውስጥ እርግጠኛ ግሳጼ አለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም ምእመናን አልነበሩም፡፡
آية رقم 140
ﭨﭩﭪﭫﭬ
ﭭ
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
آية رقم 141
ﭮﭯﭰ
ﭱ
ሰሙድ መልክተኞችን አስተባበለች፡፡
آية رقم 142
ወንድማቸው ሷሊህ ለእነርሱ ባላቸው ጊዜ «አትጠነቀቁምን
آية رقم 143
ﭺﭻﭼﭽ
ﭾ
«እኔ ለእናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡
آية رقم 144
ﭿﮀﮁ
ﮂ
«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡
آية رقم 145
«በእርሱም ላይ ምንም ዋጋ አልለምናችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡
آية رقم 146
ﮐﮑﮒﮓﮔ
ﮕ
«በዚያ እዚህ ባለው (ጸጋ) ውስጥ የረካችሁ ኾናችሁ ትተዋላችሁን
آية رقم 147
ﮖﮗﮘ
ﮙ
«በአትክልቶችና በምንጮች ውስጥ፡፡
آية رقم 148
ﮚﮛﮜﮝ
ﮞ
«በአዝመራዎችም ፍሬዋ የበሰለ በኾነች ዘንባባም፤ (ውስጥ ትተዋላችሁን)
آية رقم 149
ﮟﮠﮡﮢﮣ
ﮤ
«ብልሆች ኾናችሁ ከጋራዎች ቤቶችንም ትጠርባላችሁ፡፡
آية رقم 150
ﮥﮦﮧ
ﮨ
«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡
آية رقم 151
ﮩﮪﮫﮬ
ﮭ
«የወሰን አላፊዎችንም ትዕዛዝ አትከተሉ፡፡
آية رقم 152
ﮮﮯﮰﮱﯓﯔ
ﯕ
«የእነዚያን በምድር ላይ የሚያጠፉትንና የማያበጁትን፡፡»
آية رقم 153
ﯖﯗﯘﯙﯚ
ﯛ
(እነሱም) አሉ «አንተ በብዙ ከተደገመባቸው ሰዎች ብቻ ነህ፡፡
آية رقم 154
«አንተ ብጤያችን ሰው እንጅ ሌላ አይደለህም፡፡ ከእውነተኞቹም እንደኾንክ ተዓምርን አምጣ፡፡»
آية رقم 155
(እርሱም) አለ «ይህች ግመል ናት፡፡ ለእርሷ የመጠጥ ፋንታ አላት፡፡ ለእናንተም የታወቀ ቀን ፋንታ አላችሁ፡፡
آية رقم 156
«በክፉም አትንኳት፡፡ የታላቅ ቀን ቅጣት ይይዛችኋልና፡፡»
آية رقم 157
ﯺﯻﯼ
ﯽ
ወጓትም፡፡ ወዲያውም ተጸጻቾች ኾነው አነጉ፡፡
آية رقم 158
ቅጣቱም ያዛቸው፡፡ በዚህም ውስጥ ግሳፄ አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም ምእመናን አልነበሩም፡፡
آية رقم 159
ﰋﰌﰍﰎﰏ
ﰐ
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
آية رقم 160
ﭑﭒﭓﭔ
ﭕ
የሉጥ ሕዝቦች መልክተኞችን አስተባባሉ፡፡
آية رقم 161
ወንድማቸው ሉጥ ለእነርሱ ባለ ጊዜ «አትጠነቀቁምን
آية رقم 162
ﭞﭟﭠﭡ
ﭢ
«እኔ ለእናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡
آية رقم 163
ﭣﭤﭥ
ﭦ
«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡
آية رقم 164
«በእርሱም ላይ ምንም ዋጋ አልለምናችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡
آية رقم 165
ﭴﭵﭶﭷ
ﭸ
«ከዓለማት ሰዎች ወንዶችን ትመጣላችሁን
آية رقم 166
«ከሚስቶቻችሁም ጌታችሁ ለናንተ የፈጠረላችሁን ትተዋላችሁን በእውነቱ እናንተ ወሰን አላፊዎች ሕዝቦ ናችሁ፡፡»
آية رقم 167
(እነርሱም) አሉ «ሉጥ ሆይ! ባትከለከል በእርግጥ (ከአገር) ከሚወጡት ትኾናለህ፡፡»
آية رقم 168
ﮏﮐﮑﮒﮓ
ﮔ
(እርሱም) አለ «እኔ ሥራችሁን ከሚጠሉት ሰዎች ነኝ፡፡
آية رقم 169
ﮕﮖﮗﮘﮙ
ﮚ
«ጌታዬ ሆይ! እኔንም ቤተሰቦቼንም ከሚሠሩት ሥራ (ቅጣት) አድነን፡፡»
آية رقم 170
ﮛﮜﮝ
ﮞ
እርሱንም ቤተሰቦቹንም በጠቅላላ አዳንናቸው፡፡
آية رقم 171
ﮟﮠﮡﮢ
ﮣ
በቀሪዎቹ ውስጥ የኾነች አሮጊት ብቻ ስትቀር (እርሷ ጠፋች)፡፡
آية رقم 172
ﮤﮥﮦ
ﮧ
ከዚያም ሌሎቹን አጠፋን፡፡
آية رقم 173
በእነሱም ላይ (የድንጋይን) ዝናምን አዘነምንባቸው፡፡ የተስፈራሪዎቹም ዝናም (ምንኛ) ከፋ፡፡
آية رقم 174
በዚህ ውስጥ አስደናቂ ተዓምር አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም ምእመናን አልነበሩም፡፡
آية رقم 175
ﯛﯜﯝﯞﯟ
ﯠ
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
آية رقم 176
ﯡﯢﯣﯤ
ﯥ
የአይከት ሰዎች መልክተኞችን አስተባበሉ፤
آية رقم 177
ﯦﯧﯨﯩﯪﯫ
ﯬ
ሹዕይብ ለእነርሱ ባላቸው ጊዜ «አትጠነቀቁምን
آية رقم 178
ﯭﯮﯯﯰ
ﯱ
«እኔ ለእናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡
آية رقم 179
ﯲﯳﯴ
ﯵ
«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡
آية رقم 180
«በርሱም ላይ ምንም ዋጋ አልጠይቃችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡
آية رقم 181
«ስፍርን ሙሉ፡፡ ከአጉዳዮቹም አትኹኑ፡፡
آية رقم 182
ﰋﰌﰍ
ﰎ
«በትክክለኛ ሚዛንም መዝኑ፡፡
آية رقم 183
«ሰዎችንም ነገሮቻቸውን አታጉድሉባቸው፡፡ በምድርም ላይ አጥፊዎች ኾናችሁ አታበላሹ፡፡
آية رقم 184
ﭑﭒﭓﭔﭕ
ﭖ
«ያንንም የፈጠራችሁን የቀድሞዎቹንም ፍጡሮች (የፈጠረውን) ፍሩ፡፡»
آية رقم 185
ﭗﭘﭙﭚﭛ
ﭜ
አሉ «አንተ በብዛት ከተደገመባቸው ሰዎች ነህ፡፡
آية رقم 186
«አንተም ብጤያችን ሰው እንጅ ሌላ አይደለህም፡፡ እነሆ ከውሸታሞች ነህ ብለን እንጠረጥርሃለን፡፡
آية رقم 187
«ከእውነተኞቹም እንደኾንክ በእኛ ላይ ከሰማይ ቁራጭን ጣልብን፡፡»
آية رقم 188
ﭱﭲﭳﭴﭵ
ﭶ
«ጌታዬ የምትሠሩትን ሁሉ ዐዋቂ ነው፤» አላቸው፡፡
آية رقم 189
አስተባበሉትም፡፡ የጥላይቷ ቀን ቅጣትም ያዛቸው፡፡ እርሱ የከባድ ቀን ቅጣት ነበርና፡፡
آية رقم 190
በዚህ ውስጥ አስደናቂ ተዓምር አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም ምእምናን አልነበሩም፡፡
آية رقم 191
ﮍﮎﮏﮐﮑ
ﮒ
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
آية رقم 192
ﮓﮔﮕﮖ
ﮗ
እርሱም (ቁርኣን) በእርግጥ ከዓለማት ጌታ የተወረደ ነው፡፡
آية رقم 193
ﮘﮙﮚﮛ
ﮜ
እርሱን ታማኙ መንፈስ (ጂብሪል) አወረደው፤
آية رقم 194
ﮝﮞﮟﮠﮡ
ﮢ
ከአስፈራሪዎቹ (ነቢያት) ትኾን ዘንድ በልብህ ላይ (አወረደው)፡፡
آية رقم 195
ﮣﮤﮥ
ﮦ
ግልጽ በኾነ ዐረብኛ ቋንቋ፡፡
آية رقم 196
ﮧﮨﮩﮪ
ﮫ
እርሱም (ቁርኣን) በቀድሞዎቹ መጻሐፍት ውስጥ (የተወሳ ነው)፡፡
آية رقم 197
የእስራኤል ልጆች ሊቃውንት የሚያውቁት መኾኑ ለእነርሱ (ለመካ ከሓዲዎች) ምልክት አይኾናቸውምን
آية رقم 198
ﯗﯘﯙﯚﯛ
ﯜ
ከአዕጀሞች ባንዱ ላይ ባወረድነውም ኖሮ፤
آية رقم 199
ﯝﯞﯟﯠﯡﯢ
ﯣ
በእነርሱ ላይ ባነበበውም በእርሱ አማኞች አይኾኑም ነበር፡፡
آية رقم 200
ﯤﯥﯦﯧﯨ
ﯩ
እንደዚሁ (ማስተባበልን) በተንኮለኞች ልቦች ውስጥ አስገባነው፡፡
آية رقم 201
አሳማሚ ቅጣትን እስከሚያዩ ድረስ በእርሱ አያምኑም፡፡
آية رقم 202
ﯲﯳﯴﯵﯶ
ﯷ
እነርሱ የማያውቁ ሲኾኑ (ቅጣቱ) ድንገት እስከሚመጣባቸውም ድረስ (አያምኑም)፡፡
آية رقم 203
ﯸﯹﯺﯻ
ﯼ
(በመጣባቸው ጊዜ) «እኛ የምንቆይ ነን» እስከሚሉም (አያምኑም)፡፡
آية رقم 204
ﯽﯾ
ﯿ
በቅጣታችን ያቻኩላሉን
آية رقم 205
ﰀﰁﰂﰃ
ﰄ
አየህን ብዙ ዓመታትን ብናጣቅማቸው፤
آية رقم 206
ﰅﰆﰇﰈﰉ
ﰊ
ከዚያም ያ ይስፈራሩበት የነበሩት ቢመጣባቸው፤
آية رقم 207
ﭑﭒﭓﭔﭕﭖ
ﭗ
ይጣቀሙበት የነበሩት ሁሉ ከእነሱ ምንም አያብቃቃቸውም፡፡
آية رقم 208
አንዲትንም ከተማ ለእርሷ አስፈራሪዎች ያሏት (እና ያስተባበለች) ኾና እንጅ አላጠፋንም፡፡
آية رقم 209
ﭠﭡﭢﭣ
ﭤ
(ይህች) ግሳፄ ናት፡፡ በዳዮችም አልነበርንም፡፡
آية رقم 210
ﭥﭦﭧﭨ
ﭩ
ሰይጣናትም እርሱን (ቁርኣንን) አላወረዱትም፡፡
آية رقم 211
ﭪﭫﭬﭭﭮ
ﭯ
ለእነርሱም አይገባቸውም፤ አይችሉምም፡፡
آية رقم 212
ﭰﭱﭲﭳ
ﭴ
እነርሱ (የመላእክትን ንግግር) ከመስማት ተከለከሉ ናቸው፡፡
آية رقم 213
ከአላህም ጋር ሌላን አምላክ አትግገዛ፤ ከሚቀጡት ትኾናለህና፡፡
آية رقم 214
ﭿﮀﮁ
ﮂ
ቅርቦች ዘመዶችህንም አስጠንቅቅ፡፡
آية رقم 215
ﮃﮄﮅﮆﮇﮈ
ﮉ
ከምእምናንም ለተከተሉህ ሰዎች ክንፍህን ዝቅ አድርግ፤ (ልዝብ ኹን)፡፡
آية رقم 216
«እንቢ» ቢሉህም «እኔ ከምትሠሩት ንጹሕ ነኝ» በላቸው፡፡
آية رقم 217
ﮒﮓﮔﮕ
ﮖ
አሸናፊ አዛኝ በኾነው (ጌታህ) ላይም ተጠጋ፡፡
آية رقم 218
ﮗﮘﮙﮚ
ﮛ
በዚያ ለሶላት በምትቆም ጊዜ በሚያይህ፡፡
آية رقم 219
ﮜﮝﮞ
ﮟ
በሰጋጆች ውስጥ መዘዋወርህንም (በሚያየው ጌታህ ላይ ተጠጋ)፡፡
آية رقم 220
ﮠﮡﮢﮣ
ﮤ
እነሆ እርሱ ሰሚው ዐዋቂው ነውና፡፡
آية رقم 221
ﮥﮦﮧﮨﮩﮪ
ﮫ
ሰይጣናት በማን ላይ እንደሚወርዱ ልንገራችሁን
آية رقم 222
ﮬﮭﮮﮯﮰ
ﮱ
በውሸታም ኀጢአተኛ ሁሉ ላይ ይወርዳሉ፡፡
آية رقم 223
ﯓﯔﯕﯖ
ﯗ
የሰሙትን (ወደ ጠንቋዮች) ይጥላሉ፡፡ አብዛኞቻቸውም ውሸታሞች ናቸው፡፡
آية رقم 224
ﯘﯙﯚ
ﯛ
ባለ ቅኔዎችንም ጠማማዎቹ ይከተሉዋቸዋል፡፡
آية رقم 225
እነርሱ በ(ንግግር) ሸለቆ ሁሉ የሚዋልሉ መኾናቸውን አታይምን
آية رقم 226
ﯤﯥﯦﯧﯨ
ﯩ
እነሱም የማይሠሩትን ነገር የሚናገሩ መኾናቸውን (አታይምን)፤
آية رقم 227
እነዚያ ያመኑና መልካም ሥራዎችን የሠሩ አላህንም በብዛት ያወሱ ከተበደሉም በኋላ (በቅኔ) የተከላከሉ ሲቀሩ፤ (እነርሱ አይወቀሱም)፡፡ እነዚያም የበደሉ (ከሞቱ በኋላ) እንዴት ያለን መመለስ እንደሚመለሱ በእርግጥ ያውቃሉ፡፡
تقدم القراءة