سورة الأعلى

الترجمة الأمهرية

ترجمة معاني سورة الأعلى باللغة الأمهرية من كتاب الترجمة الأمهرية

محمد صادق

الترجمة الأمهرية

محمد صادق

آية رقم 1
ከሁሉ በላይ የኾነውን ጌታህን ስም አሞግሥ፡፡
آية رقم 2
የዚያን (ሁሉን ነገር) የፈጠረውን ያስተካከለውንም፡፡
آية رقم 3
የዚያንም የወሰነውን፡፡ (ለተፈጠረለት ነገር) የመራውንም፡፡
آية رقم 4
የዚያንም ግጦሽን (ለምለም አድርጎ) ያወጣውን፡፡
آية رقم 5
(ከዚያ) ደረቅ ጥቁር ያደረገውንም (አምላክ ስም አሞግስ)፡፡
آية رقم 6
(ቁርኣንን) በእርግጥ እናስነብብሃለን፤ አትረሳምም፡፡
አላህ ከሻው ነገር በስተቀር፡፡ እርሱ ግልጹን የሚሸሸገውንም ሁሉ ያውቃልና፡፡
آية رقم 8
ለገሪቱም (ሕግጋት) እንገጥምሃለን፡፡
آية رقم 9
ግሣጼይቱ ብትጠቅም (ሰዎችን) ገሥጽም፡፡
آية رقم 10
(አላህን) የሚፈራ ሰው በእርግጥ ይገሠጻል፡፡
آية رقم 11
መናጢውም ይርቃታል፡፡
آية رقم 12
ያ ታላቂቱን እሳት የሚገባው፡፡
آية رقم 13
ከዚያም በእርሷ ውስጥ አይሞትም ሕያውም አይኾንም፡፡
آية رقم 14
የተጥራራ ሰው በእርግጥ ዳነ፡፡
آية رقم 15
የጌታውንም ስም ያወሳና የሰገደ፡፡
آية رقم 16
ይልቁንም ቅርቢቱን ሕይወት ትመርጣላችሁ፡፡
آية رقم 17
መጨረሻይቱ (ሕይወት) በላጭ ሁል ጊዜ ዘውታሪም ስትኾን፡፡
آية رقم 18
ይህ በፊተኞቹ መጻሕፍት ውስጥ ያልለ ነው፡፡
آية رقم 19
በኢብራሂምና በሙሳ ጽሑፎች ውስጥ፡፡
تقدم القراءة