የሱራ الذاريات ትርጉም በالأمهرية ከSadiq and Sani - Amharic translation
Verse 1
ﯤﯥ
ﯦ
መበተንን በታኞች በኾኑት (ነፋሶች)፡፡
Verse 2
ﯧﯨ
ﯩ
ከባድ (ዝናምን) ተሸካሚዎች በኾኑትም (ደመናዎች)፡፡
Verse 3
ﯪﯫ
ﯬ
ገር (መንሻለልን) ተንሻላዮች በኾኑትም (መርከቦች)፡፡
Verse 4
ﯭﯮ
ﯯ
ነገርን ሁሉ አከፋፋዮች በኾኑትም (መላእክት) እምላለሁ፡፡
Verse 5
ﯰﯱﯲ
ﯳ
የምትቀጠሩት (ትንሣኤ) እውነት ነው፡፡
Verse 6
ﯴﯵﯶ
ﯷ
(እንደየሥራው) ዋጋን ማግኘትም፤ ኋኝ ነው፤ (የማይቀር ነው)፡፡
Verse 7
ﭑﭒﭓ
ﭔ
የ(ከዋክብት) መንገዶች ባለቤት በኾነችው ሰማይ እምላለሁ፡፡
Verse 8
ﭕﭖﭗﭘ
ﭙ
እናንተ (የመካ ሰዎች) በተለያየ ቃል ውስጥ ናችሁ፡፡
Verse 9
ﭚﭛﭜﭝ
ﭞ
ከርሱ የሚዝዞር ሰው ይዝዞራል፡፡
Verse 10
ﭟﭠ
ﭡ
በግምት የሚናገሩ ውሸታሞች ተረገሙ፡፡
Verse 11
ﭢﭣﭤﭥﭦ
ﭧ
እነዚያ እነርሱ በሚሸፍን ስሕተተ ውስጥ ዘንጊዎች የኾኑት፡፡
Verse 12
ﭨﭩﭪﭫ
ﭬ
የዋጋ መስጫው ቀን መቼ እንደ ኾነ ይጠይቃሉ፡፡
Verse 13
ﭭﭮﭯﭰﭱ
ﭲ
(እነርሱ) በእሳት ላይ በሚፈተኑበት ቀን ነው፡፡
Verse 14
«መከራችሁን ቅመሱ፤ ይህ ያ በእርሱ ትቻኮሉበት የነበራችሁት ነው» (ይባላሉ)፡፡
Verse 15
ﭻﭼﭽﭾﭿ
ﮀ
አላህን ፈሪዎቹ በአትክልቶችና በምንጮች ውስጥ ናቸው፡፡
Verse 16
ያንን ጌታቸው የሰጣቸውን ተቀባዮች ኾነው፤ (በገነት ውስጥ ይኾናሉ)፡፡ እነርሱ ከዚህ በፊት መልካም ሰሪዎች ነበሩና፡፡
Verse 17
ﮌﮍﮎﮏﮐﮑ
ﮒ
ከሌሊቱ ጥቂትን ብቻ ይተኙ ነበሩ፡፡
Verse 18
ﮓﮔﮕ
ﮖ
በሌሊቱ መጨረሻዎችም እነርሱ ምሕረትን ይለምናሉ፡፡
Verse 19
ﮗﮘﮙﮚﮛ
ﮜ
በገንዘቦቻቸውም ውስጥ ለለማኝና (ከልመና) ለተከለከለም (በችሮታቸው) መብት አልለ፡፡
Verse 20
ﮝﮞﮟﮠ
ﮡ
በምድርም ውስጥ ለሚያረጋግጡ ሰዎች ምልክቶች አልሉ፡፡
Verse 21
ﮢﮣﮤﮥﮦ
ﮧ
በነፍሶቻችሁም ውስጥ (ምልክቶች አልሉ)፤ ታዲያ አትመለከቱምን?›
Verse 22
ﮨﮩﮪﮫﮬ
ﮭ
ሲሳያችሁም የምትቀጠሩትም (ፍዳና ምንዳ) በሰማይ ውስጥ ነው፡፡
Verse 23
በሰማይና በምድር ጌታም እምላለሁ፡፡ እርሱ እናንተ እንደምትናገሩት ብጤ እርግጠኛ ነው፡፡
Verse 24
ﯙﯚﯛﯜﯝﯞ
ﯟ
የተከበሩት የኢብራሂም እንግዶች ወሬ መጥቶሃልን?
Verse 25
በእርሱ ላይ በገቡና «ሰለም» ባሉ ጊዜ (አስታውስ)፡፡ «ሰላም ያልታወቃችሁ ሕዝቦች ናችሁ፤» አላቸው፡፡
Verse 26
ﯫﯬﯭﯮﯯﯰ
ﯱ
ወደ ቤተሰቡም ተዘነበለ፤» ወዲያውም የሰባ ወይፈንን አመጣ፡፡
Verse 27
ﯲﯳﯴﯵﯶ
ﯷ
ወደእነርሱም (አርዶና ጠብሶ) አቀረበው፡፡ «አትበሉም ወይ?» አላቸው፡፡
Verse 28
ከእነርሱ መፍራትንም በልቡ አሳደረ፡፡ «አትፍራ» አሉት፡፡ በዐዋቂ ወጣት ልጅም አበሰሩት፡፡
Verse 29
ሚስቱም እየጮኸች መጣች፡፡ ፊቷንም መታች፡፡ «መካን አሮጊት ነኝ» አለችም፡፡
Verse 30
እንደዚህ ጌታሽ ብሏል፡፡ «እነሆ እርሱ ጥበባ ዐዋቂ ነውና» አሏት፡፡
Verse 31
ﭑﭒﭓﭔﭕﭖ
ﭗ
«እናንተ መልክተኞች ሆይ! ታዲያ ነገራችሁ ምንድን ነው?» አላቸው፡፡
Verse 32
ﭘﭙﭚﭛﭜﭝ
ﭞ
(እነርሱም) አሉ፡- «እኛ ወደ አመጸኞች ሕዝቦች ተልከናል፡፡»
Verse 33
ﭟﭠﭡﭢﭣ
ﭤ
በእነርሱ ላይ ከጭቃ የኾኑን ድንጋዮች ልንለቅባቸው (ተላክን)፡፡
Verse 34
ﭥﭦﭧﭨ
ﭩ
በጌታህ ዘንድ ለድንበር አላፊዎቹ (በየስማቸው) ምልክት የተደረገባት ስትኾን፡፡
Verse 35
ﭪﭫﭬﭭﭮﭯ
ﭰ
ከምእምናንም፤ በእርሷ (በከተማቸው) ውስጥ የነበሩትን አወጣን፡፡
Verse 36
በውስጧም ከሙስሊሞች ከአንድ ቤት (ቤተሰቦች) በስተቀር አላገኘንም፡፡
Verse 37
በውስጧም ለእነዚያ አሳማሚውን ቅጣት ለሚፈሩት ምልክትን አስቀረን፡፡
Verse 38
በሙሳም (ወሬ) ውስጥ ወደ ፈርዖን በግልጽ ማስረጃ በላክነው ጊዜ (ምልክትን አደረግን)፡፡
Verse 39
ﮊﮋﮌﮍﮎﮏ
ﮐ
ከድጋፉ (ከሰራዊቱ) ጋርም (ከእምነት) ዞረ፡፡ (እርሱ) «ድግምተኛ ወይም ዕብድ ነው» አለም፡፡
Verse 40
እርሱንም ሰራዊቱንም ያዝናቸው፡፡ እርሱ ተወቃሽ ሲኾን በባሕር ውስጥም ጣልናቸው፡፡
Verse 41
በዓድም በእነርሱ ላይ መካንን ነፋስ በላክን ጊዜ (ምልክት አልለ)፡፡
Verse 42
በላዩ ላይ የመጣችበትን ማንኛውንም ነገር እንደ በሰበሰ አጥንት ያደረገችው ብትኾን እንጂ አትተወውም፡፡
Verse 43
በሰሙድም ለእነርሱ «እስከ ጊዜ (ሞታችሁ) ድረስ ተጣቀሙ» በተባሉ ጊዜ (ምልክት አልለ)፡፡
Verse 44
ከጌታቸው ትዕዛዝም ኮሩ፡፡ እነርሱም እያዩ ጩኸት ያዘቻቸው፡፡
Verse 45
መቆምንም ምንም አልቻሉም፡፡ የሚርረዱም አልነበሩም፡፡
Verse 46
የኑሕንም ሕዝቦች ከዚህ በፊት (አጠፋን)፡፡ እነርሱ አመጸኞች ሕዝቦች ነበሩና፡፡
Verse 47
ﯰﯱﯲﯳﯴ
ﯵ
ሰማይንም በኀይል ገነባናት፡፡ እኛም በእርግጥ ቻዮች ነን፡፡
Verse 48
ﯶﯷﯸﯹ
ﯺ
ምድርንም ዘረጋናት፡፡ ምን ያማርንም ዘርጊዎች (ነን!)
Verse 49
ትገነዘቡም ዘንድ ከነገሩ ሁሉ ሁለት (ተቃራኒ) ዓይነትን ፈጠርን፡፡
Verse 50
«ወደ አላህም ሽሹ፤ እኔ ለእናንተ ከርሱ ግልጽ አስጠንቃቂ ነኝና» (በላቸው)፡፡
Verse 51
ከአላህም ጋር ሌላን አምላክ አታድርጉ፡፡ እኔ ለእናንተ ከእርሱ (የተላክሁ) ግልጽ አስፈራሪ ነኝና፡፡
Verse 52
(ነገሩ) እንደዚሁ ነው፡፡ እነዚያን ከእነርሱ በፊት የነበሩትን ከመልክተኛ ማንም አልመጣቸውም፡፡ (እርሱ) «ድግምተኛ ወይም ዕብድ ነው» ያሉ ቢኾኑ እንጂ፡፡
Verse 53
በእርሱ (በዚህ ቃል) አደራ ተባብለዋልን? አይደለም፤ እነርሱ ጥጋበኞች ሕዝቦች ናቸው፡፡
Verse 54
ﭧﭨﭩﭪﭫ
ﭬ
ከእነርሱም (ክርክር) ዘወር በል፤ (ተዋቸው)፡፡ አንተ ምንም ተወቃሽ አይደለህምና፡፡
Verse 55
ﭭﭮﭯﭰﭱ
ﭲ
ገሥጽም፤ ግሣጼ ምእመናንን ትጠቅማለችና፡፡
Verse 56
ﭳﭴﭵﭶﭷﭸ
ﭹ
ጋኔንንና ሰውንም ሊግገዙኝ እንጅ ለሌላ አልፈጠርኳቸውም፡፡
Verse 57
ከነርሱም ምንም ሲሳይ አልፈልግም፡፡ ሊመግቡኝም አልሻም፡፡
Verse 58
አላህ እርሱ ሲሳይን ሰጪ የብርቱ ኀይል ባለቤት ነው፡፡
Verse 59
ለእነዚያም ለበደሉት እንደ ጓደኞቻቸው ፋንታ ብጤ (የቅጣት) ፋንታ አልላቸው፡፡ ስለዚህ አያስቸኩሉኝ፡፡
Verse 60
ለነዚያም ለካዱት ከዚያ ከሚቀጠሩት ቀናቸው ወዮላቸው፡
تقدم القراءة