surah.translation .
من تأليف: محمد صادق ومحمد الثاني حبيب .

በዝሆኑ ባለቤቶች ጌታህ እንዴት እንደሠራ አላወቅህምን?
ተንኮላቸውን በጥፋት ውስጥ (ከንቱ) አላደረገምን? (አድርጓል)፡፡
በእነርሱም ላይ መንጎች የኾኑን ዎፎች ላከ፡፡
ከተጠበሰ ጭቃ በኾነ ድንጋይ የምትወረውርባቸው የኾነችን፤ (አዕዋፍ)፡፡
ቅጠሉ እንደ ተበላ አዝመራም አደረጋቸው፡፡