سورة الشمس

الترجمة الأمهرية

የሱራ الشمس ትርጉም በالأمهرية ከالترجمة الأمهرية

الترجمة الأمهرية

Verse 1
በፀሐይና በብርሃኗ እምላለሁ፡፡
Verse 3
በቀኑም (ፀሐይን) በገለጻት ጊዜ፤
Verse 5
በሰማይቱም በገነባትም (ጌታ)፤
Verse 8
አመጽዋንና ፍርሃትዋንም ባሳወቃት (አምላክ እምላለሁ)፡፡
Verse 9
(ከኀጢኣት) ያጠራት ሰው ፍላጎቱን በእርግጥ አገኘ፡፡
Verse 10
(በኀጢኣት) የሸፈናትም ሰው በእውነት አፈረ፡፡
Verse 11
ሠሙድ ወሰን በማለፍዋ አስተባበለች፡፡
Verse 12
ጠማማዋ በተንቀሳቀሰ ጊዜ፡፡
ለእነርሱም የአላህ መልክተኛ (ሷሊህ) «የአላህን ግመል የመጠጥ ተራዋንም (ተጠንቀቁ)» አላቸው፡፡
አስተባበሉትም፡፡ (ቋንጃዋን) ወጓትም፡፡ በኀጢኣታቸውም ምክንያት ጌታቸው (ቅጣትን) በእነርሱ ላይ ደመደመባቸው፤ አስተካከላትም፡፡
Verse 15
ፍጻሜዋንም (የምታስከትለውን) አያፈራም፡፡
تقدم القراءة