የሱራ الشمس ትርጉም በالأمهرية ከالترجمة الأمهرية
Verse 1
ﭜﭝ
ﭞ
በፀሐይና በብርሃኗ እምላለሁ፡፡
Verse 2
ﭟﭠﭡ
ﭢ
በጨረቃም በተከተላት ጊዜ፤
Verse 3
ﭣﭤﭥ
ﭦ
በቀኑም (ፀሐይን) በገለጻት ጊዜ፤
Verse 4
ﭧﭨﭩ
ﭪ
በሌሊቱም በሸፈናት ጊዜ፤
Verse 5
ﭫﭬﭭ
ﭮ
በሰማይቱም በገነባትም (ጌታ)፤
Verse 6
ﭯﭰﭱ
ﭲ
በምድሪቱም በዘረጋትም፤
Verse 7
ﭳﭴﭵ
ﭶ
በነፍስም ባስተካከላትም፤
Verse 8
ﭷﭸﭹ
ﭺ
አመጽዋንና ፍርሃትዋንም ባሳወቃት (አምላክ እምላለሁ)፡፡
Verse 9
ﭻﭼﭽﭾ
ﭿ
(ከኀጢኣት) ያጠራት ሰው ፍላጎቱን በእርግጥ አገኘ፡፡
Verse 10
ﮀﮁﮂﮃ
ﮄ
(በኀጢኣት) የሸፈናትም ሰው በእውነት አፈረ፡፡
Verse 11
ﮅﮆﮇ
ﮈ
ሠሙድ ወሰን በማለፍዋ አስተባበለች፡፡
Verse 12
ﮉﮊﮋ
ﮌ
ጠማማዋ በተንቀሳቀሰ ጊዜ፡፡
Verse 13
ለእነርሱም የአላህ መልክተኛ (ሷሊህ) «የአላህን ግመል የመጠጥ ተራዋንም (ተጠንቀቁ)» አላቸው፡፡
Verse 14
አስተባበሉትም፡፡ (ቋንጃዋን) ወጓትም፡፡ በኀጢኣታቸውም ምክንያት ጌታቸው (ቅጣትን) በእነርሱ ላይ ደመደመባቸው፤ አስተካከላትም፡፡
Verse 15
ﮝﮞﮟ
ﮠ
ፍጻሜዋንም (የምታስከትለውን) አያፈራም፡፡
تقدم القراءة