سورة القيامة

الترجمة الأمهرية

የሱራ القيامة ትርጉም በالأمهرية ከالترجمة الأمهرية

الترجمة الأمهرية

Verse 1
(ነገሩ ከሓዲዎች እንደሚሉት) አይደለም፡፡ በትንሣኤ ቀን እምላለሁ፡፡
Verse 2
(ራሷን) ወቃሽ በኾነች ነፍስም እምላለሁ፡፡ (በእርግጥ ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡
ሰው አጥንቶቹን አለመሰብሰባችንን ያስባልን?
አይደለም ጣቶቹን (ፊት እንደ ነበሩ) በማስተካከል ላይ ቻዮች ስንኾን (እንሰበስባቸዋለን)፡፡
ይልቁንም ሰው በፊቱ ባለው ነገር (በትንሣኤ) ሊያስተባብል ይፈልጋል፡፡
Verse 6
«የትንሣኤው ቀን መቼ ነው?» ሲል ይጠይቃል፡፡
Verse 8
ጨረቃም በጨለመ ጊዜ፡፡
Verse 9
ፀሐይና ጨረቃም በተሰበሰቡ ጊዜ፡፡
«ሰው በዚያ ቀን መሸሻው የት ነው?» ይላል፡፡
Verse 11
ይከልከል፤ ምንም መጠጊያ የለም፡፡
Verse 12
በዚያ ቀን መርጊያው ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡
ሰው በዚያ ቀን ባስቀደመውና ባስቆየው ሁሉ ይነገራል፡፡
በእርግጥም ሰው በነፍሱ ላይ አስረጅ ነው፡፡ (አካሎቹ ይመሰክሩበታል)፡፡
Verse 15
ምክንያቶቹን ሁሉ ቢያመጣም እንኳ (አይሰማም)፡፡
በእርሱ (በቁርኣን ንባብ) ልትቸኩል ምላስህን በእርሱ አታላውስ፡፡
Verse 17
(በልብህ ውስጥ) መሰብሰቡና ማንበቡ በእኛ ላይ ነውና፡፡
Verse 18
ባነበብነውም ጊዜ (ካለቀ በኋላ) ንባቡን ተከተል፡፡
Verse 19
ከዚያም ማብራራቱ በእኛ ላይ ነው፡፡
Verse 20
(ከመጣደፍ) ተከልከል፡፡ ይልቁንም (ሰዎች) ፈጣኒቱን (ዓለም) ትወዳላችሁ፡፡
Verse 21
መጨረሻይቱንም (ዓለም) ትተዋላችሁ፡፡ (አትዘጋጁላትም)፡፡
Verse 22
ፊቶች በዚያ ቀን አብሪዎች ናቸው፡፡
Verse 23
ወደ ጌታቸው ተመልካቾች ናቸው፡፡
Verse 24
ፊቶችም በዚያ ቀን ጨፍጋጊዎች ናቸው፡፡
በርሳቸውም ዐደጋ እንደሚሠራባቸው ያረጋግጣሉ፡፡
Verse 26
ንቁ (ነፍስ) ብሪዎችን በደረሰች ጊዜ፤
Verse 28
(ሕመምተኛው) እርሱ (የሰፈረበት ነገር ከዚህ ዓለም) መልለየት መኾኑን ባረጋገጠም ጊዜ፡፡
Verse 29
ባትም በባት በተጣበቀች ጊዜ፡፡
Verse 30
በዚያ ቀን መነዳቱ ወደ ጌታህ (ፍርድ) ነው፡፡
Verse 32
ግን አስተባበለ፤ (ከእምነት) ዞረም፡፡
ከዚያም እየተንጎባለለ ወደ ቤተሰቡ ኼደ፡፡
Verse 34
የምትጠላውን ነገር (አላህ) ያስከትልህ፡፡ ለአንተ ተገቢህም ነው፡፡
Verse 35
ከዚያም ጥፋት ይጠጋህ ለአንተ የተገባህም ነው፡፡
ከዚያም የረጋ ደም ኾነ (አላህ ሰው አድርጎ) ፈጠረውም፡፡ አስተካከለውም፡፡
ከእርሱም ሁለት ዓይነቶችን ወንድና ሴትን አደረገ፡፡
تقدم القراءة