سورة الواقعة

الترجمة الأمهرية

የሱራ الواقعة ትርጉም በالأمهرية ከالترجمة الأمهرية

الترجمة الأمهرية

Verse 2
ለመውደቋ አስተባባይ (ነፍስ) የለችም፡፡
Verse 3
ዝቅ አድራጊና ከፍ አድራጊ ናት፡፡
Verse 5
ተራራዎችም መፍፈርፈርን በተፈረፈሩ ጊዜ (እንደተፈጨ ዱቄት በኾኑ ጊዜ)፡፡
Verse 7
ሦስት ዓይነቶችም በኾናችሁ ጊዜ (ታዋርዳለች፤ ታነሳለችም)፡፡
የቀኝ ጓዶችም ምን (የተከበሩ) የቀኝ ጓዶች ናቸው፡፡
የግራ ጓዶችም ምን (የተዋረዱ) የግራ ጓዶች ናቸው፡፡
Verse 10
(ለበጎ ሥራ) ቀዳሚዎቹም (ለገነት) ቀዳሚዎች ናቸው፡፡
Verse 11
እነዚያ ባለሟሎቹ ናቸው፡፡
Verse 12
በመጠቀሚያ ገነቶች ውስጥ ሲኾኑ፡፡
Verse 13
ከፊተኞቹ ብዙ ጭፍሮች ናቸው፡፡
Verse 14
ከኋለኞቹም ጥቂቶች ናቸው፡፡
Verse 15
በተታቱ አልጋዎች ላይ ይኾናሉ፡፡
Verse 16
በእርሷ ላይ የተመቻቹና ፊት ለፊት የተቅጣጩ ሲኾኑ፡፡
Verse 17
በእነርሱ ላይ ሁል ጊዜ የማያረጁ ወጣቶች ልጆች ይዘዋወራሉ፡፡
ከጠጅ ምንጭም በብርጭቆዎችና በኩስኩስቶች በጽዋም (በእነርሱ ላይ ይዝዞራሉ)፡፡
ከእርሷ የራስ ምታት አያገኛቸውም፤ አይሰክሩምም፡፡
Verse 20
ከሚመርጡትም ዓይነት በእሸቶች፡፡
Verse 21
ከሚሹትም በኾነ የበራሪ ሥጋ (ይዞሩባቸዋል)፡፡
Verse 22
ዓይናማዎች የኾኑ ነጫጭ ቆንጆዎችም አሏቸው፡፡
Verse 23
ልክ እንደተሸፈነ ሉል መሰሎች የኾኑ፡፡
Verse 24
በዚያ ይሠሩት በነበሩት ምክንያት ዋጋ ይኾን ዘንድ (ይህንን አደረግንላቸው)፡፡
በውስጥዋ ውድቅ ንግግርንና መውወንጀልን አይሰሙም፡፡
Verse 28
በተቀፈቀፈ (እሾህ በሌለው) ቁርቁራ ውስጥ ናቸው፡፡
Verse 29
(ፍሬው) በተነባበረ በሙዝ ዛፍም፡፡
Verse 30
በተዘረጋ ጥላ ሥርም፡፡
Verse 31
በሚንቧቧ ውሃ አጠገብም፡፡
Verse 32
ብዙ (ዓይነት) በኾኑ ፍራፍሬዎችም፡፡
Verse 33
የማትቋረጥም የማትከለከልም የኾነች፡፡
Verse 34
ከፍ በተደረጉ ምንጣፎችም (ሴቶችም መካከል)፡፡
Verse 35
እኛ አዲስ ፍጥረት አድርገን (ለእነርሱ) ፈጠርናቸው፡፡
Verse 36
ደናግሎችም አደረግናቸው፡፡
Verse 37
ለባሎቻቸው ተሽሞርሟሪዎች እኩያዎች (አደረግናቸው)፡፡
Verse 38
ለቀኝ ጓዶች (አዘጋጀናቸው)፡፡
Verse 39
ከፊተኞቹ ብዙ ጭፍሮች ናቸው፡፡
Verse 40
ከኋለኞቹም ብዙ ጭፍሮች ናቸው፡፡
የግራ ጓደኞችም ምንኛ (የተዋረዱ) የግራ ጓዶች! ናቸው፡፡
Verse 42
በመርዛም ነፋስ በጣም በፈላ ውሃም ውስጥ ናቸው፡፡
Verse 43
ከጥቁር ጭስም በኾነ ጥላ ውስጥ፡፡
በታላቅ ኀጢአትም ላይ ይዘወትሩ ነበሩና፡፡
ይሉም ነበሩ፡- «በሞትንና ዐፈር፣ ዐጥንቶችም በኾን ጊዜ እኛ በእርግጥ የምንቀሰቀስ ነን?
Verse 48
«የፊተኞቹ አባቶቻችንም?»
«በተወሰነ ቀን ቀጠሮ በእርግጥ ተሰብሳቢዎች ናቸው፡፡
«ከዚያም እናንተ ጠማሞች አስተባባዮች ሆይ!
Verse 53
«ከእርሷም ሆዶቻችሁን ሞይዎች ናችሁ፡፡
Verse 54
«በእርሱ ላይም ከፈላ ውሃ ጠጪዎች ናችሁ፡፡
Verse 55
«የተጠሙንም ግመሎች አጠጣጥ ብጤ ጠጪዎች ናችሁ፡፡»
Verse 56
ይህ በፍርዱ ቀን መስተንግዷቸው ነው፡፡
Verse 58
(በማኅፀኖች) የምታፈሱትን አያችሁን?
እናንተ ትፈጥሩታላችሁን? ወይስ እኛ ፈጣሪዎቹን ነን?
እኛ ሞትን (ጊዜውን) በመካከላችሁ ወሰንን፡፡ እኛም ተሸናፊዎች አይደለንም፡፡
ብጤዎቻችሁን በመለወጥና በዚያ በማታውቁትም (ቅርጽ) እናንተን በመፍጠር ላይ (አንሸነፍም)፡፡
የፊተኛይቱንም አፈጣጠር በእርግጥ ዐውቃችኋል፡፡ አትገነዘቡምን?
እናንተ ታበቅሉታላችሁን? ወይስ እኛ አብቃዮቹ ነን?
ብነሻ ኖሮ ደረቅ ስብርብር ባደረግነውና የምትደነቁም በኾናችሁ ነበር፡፡
Verse 66
«እኛ በዕዳ ተያዦች ነን፡፡
Verse 67
«በእርግጥም እኛ (ከመጠቀም) የተከለከልን ነን» (ትሉ ነበር)፡፡
Verse 68
ያንንም የምትጠጡትን ውሃ አየችሁን?
እናንተ ከደመናው አወረዳችሁትን? ወይስ እኛ አውራጆቹ ነን?
ብንሻ ኖሮ መርጋጋ ባደረግነው ነበር፡፡ አታመሰግኑምን?
Verse 71
ያቺንም የምትሰብቋትን እሳት አያችሁን?
እናንተ ዛፏን ፈጠራችሁን? ወይስ እኛ ፈጣሪዎችዋ ነን?
እኛ (ለገሀናም) ማስታወሻ ለመንገደኞችም መጠቀሚያ አደረግናት፡፡
Verse 77
እርሱ የከበረ ቁርኣን ነው፡፡
Verse 78
በተጠበቀ መጽሐፍ ውስጥ ነው፡፡
Verse 79
የተጥራሩት እንጅ ሌላ አይነካውም፡፡
Verse 81
በዚህ ንግግር እናንተ ቸልተኞች ናችሁን?
Verse 82
ሲሳያችሁንም (ዝናምን) እናንተ የምታስተባብሉት ታደርጋላችሁን?
Verse 84
እናንተ ያን ጊዜ የምታዩ ስትኾኑ፡፡
እኛም ግን አታዩም እንጅ ከእናንተ ይልቅ ወደእርሱ የቀረብን ስንኾን፡፡
Verse 87
እውነተኞች እንደ ኾናችሁ (ነፍሲቱን ወደ አካሉ) ለምን አትመልሷትም፡፡
Verse 89
(ለእርሱ) ዕረፍት፣ መልካም ሲሳይም፣ የመጠቀሚያ ገነትም አልለው፡፡
ከቀኝ ጓዶች ስለ ኾንክ ላንተ ሰላም አልለህ (ይባላል)፡፡
Verse 93
ከፈላ ውሃ የኾነ መስተንግዶ አልለው፡፡
Verse 94
በገሀነም መቃጠልም (አልለው)፡፡
تقدم القراءة