የሱራ الواقعة ትርጉም በالأمهرية ከالترجمة الأمهرية
Verse 1
ﮃﮄﮅ
ﮆ
መከራይቱ በወደቀች ጊዜ፡፡
Verse 2
ﮇﮈﮉ
ﮊ
ለመውደቋ አስተባባይ (ነፍስ) የለችም፡፡
Verse 3
ﮋﮌ
ﮍ
ዝቅ አድራጊና ከፍ አድራጊ ናት፡፡
Verse 4
ﮎﮏﮐﮑ
ﮒ
ምድር መናወጥን በተናወጠች ጊዜ፡፡
Verse 5
ﮓﮔﮕ
ﮖ
ተራራዎችም መፍፈርፈርን በተፈረፈሩ ጊዜ (እንደተፈጨ ዱቄት በኾኑ ጊዜ)፡፡
Verse 6
ﮗﮘﮙ
ﮚ
የተበተነ ብናኝ በኾኑም ጊዜ
Verse 7
ﮛﮜﮝ
ﮞ
ሦስት ዓይነቶችም በኾናችሁ ጊዜ (ታዋርዳለች፤ ታነሳለችም)፡፡
Verse 8
ﮟﮠﮡﮢﮣ
ﮤ
የቀኝ ጓዶችም ምን (የተከበሩ) የቀኝ ጓዶች ናቸው፡፡
Verse 9
ﮥﮦﮧﮨﮩ
ﮪ
የግራ ጓዶችም ምን (የተዋረዱ) የግራ ጓዶች ናቸው፡፡
Verse 10
ﮫﮬ
ﮭ
(ለበጎ ሥራ) ቀዳሚዎቹም (ለገነት) ቀዳሚዎች ናቸው፡፡
Verse 11
ﮮﮯ
ﮰ
እነዚያ ባለሟሎቹ ናቸው፡፡
Verse 12
ﮱﯓﯔ
ﯕ
በመጠቀሚያ ገነቶች ውስጥ ሲኾኑ፡፡
Verse 13
ﯖﯗﯘ
ﯙ
ከፊተኞቹ ብዙ ጭፍሮች ናቸው፡፡
Verse 14
ﯚﯛﯜ
ﯝ
ከኋለኞቹም ጥቂቶች ናቸው፡፡
Verse 15
ﯞﯟﯠ
ﯡ
በተታቱ አልጋዎች ላይ ይኾናሉ፡፡
Verse 16
ﯢﯣﯤ
ﯥ
በእርሷ ላይ የተመቻቹና ፊት ለፊት የተቅጣጩ ሲኾኑ፡፡
Verse 17
ﭑﭒﭓﭔ
ﭕ
በእነርሱ ላይ ሁል ጊዜ የማያረጁ ወጣቶች ልጆች ይዘዋወራሉ፡፡
Verse 18
ﭖﭗﭘﭙﭚ
ﭛ
ከጠጅ ምንጭም በብርጭቆዎችና በኩስኩስቶች በጽዋም (በእነርሱ ላይ ይዝዞራሉ)፡፡
Verse 19
ﭜﭝﭞﭟﭠ
ﭡ
ከእርሷ የራስ ምታት አያገኛቸውም፤ አይሰክሩምም፡፡
Verse 20
ﭢﭣﭤ
ﭥ
ከሚመርጡትም ዓይነት በእሸቶች፡፡
Verse 21
ﭦﭧﭨﭩ
ﭪ
ከሚሹትም በኾነ የበራሪ ሥጋ (ይዞሩባቸዋል)፡፡
Verse 22
ﭫﭬ
ﭭ
ዓይናማዎች የኾኑ ነጫጭ ቆንጆዎችም አሏቸው፡፡
Verse 23
ﭮﭯﭰ
ﭱ
ልክ እንደተሸፈነ ሉል መሰሎች የኾኑ፡፡
Verse 24
ﭲﭳﭴﭵ
ﭶ
በዚያ ይሠሩት በነበሩት ምክንያት ዋጋ ይኾን ዘንድ (ይህንን አደረግንላቸው)፡፡
Verse 25
ﭷﭸﭹﭺﭻﭼ
ﭽ
በውስጥዋ ውድቅ ንግግርንና መውወንጀልን አይሰሙም፡፡
Verse 26
ﭾﭿﮀﮁ
ﮂ
ግን ሰላም መባባልን (ይሰማሉ)፡፡
Verse 27
ﮃﮄﮅﮆﮇ
ﮈ
የቀኝም ጓዶች ምንኛ (የከበሩ) የቀኝ ጓዶች!
Verse 28
ﮉﮊﮋ
ﮌ
በተቀፈቀፈ (እሾህ በሌለው) ቁርቁራ ውስጥ ናቸው፡፡
Verse 29
ﮍﮎ
ﮏ
(ፍሬው) በተነባበረ በሙዝ ዛፍም፡፡
Verse 30
ﮐﮑ
ﮒ
በተዘረጋ ጥላ ሥርም፡፡
Verse 31
ﮓﮔ
ﮕ
በሚንቧቧ ውሃ አጠገብም፡፡
Verse 32
ﮖﮗ
ﮘ
ብዙ (ዓይነት) በኾኑ ፍራፍሬዎችም፡፡
Verse 33
ﮙﮚﮛﮜ
ﮝ
የማትቋረጥም የማትከለከልም የኾነች፡፡
Verse 34
ﮞﮟ
ﮠ
ከፍ በተደረጉ ምንጣፎችም (ሴቶችም መካከል)፡፡
Verse 35
ﮡﮢﮣ
ﮤ
እኛ አዲስ ፍጥረት አድርገን (ለእነርሱ) ፈጠርናቸው፡፡
Verse 36
ﮥﮦ
ﮧ
ደናግሎችም አደረግናቸው፡፡
Verse 37
ﮨﮩ
ﮪ
ለባሎቻቸው ተሽሞርሟሪዎች እኩያዎች (አደረግናቸው)፡፡
Verse 38
ﮫﮬ
ﮭ
ለቀኝ ጓዶች (አዘጋጀናቸው)፡፡
Verse 39
ﮮﮯﮰ
ﮱ
ከፊተኞቹ ብዙ ጭፍሮች ናቸው፡፡
Verse 40
ﯓﯔﯕ
ﯖ
ከኋለኞቹም ብዙ ጭፍሮች ናቸው፡፡
Verse 41
ﯗﯘﯙﯚﯛ
ﯜ
የግራ ጓደኞችም ምንኛ (የተዋረዱ) የግራ ጓዶች! ናቸው፡፡
Verse 42
ﯝﯞﯟ
ﯠ
በመርዛም ነፋስ በጣም በፈላ ውሃም ውስጥ ናቸው፡፡
Verse 43
ﯡﯢﯣ
ﯤ
ከጥቁር ጭስም በኾነ ጥላ ውስጥ፡፡
Verse 44
ﯥﯦﯧﯨ
ﯩ
ቀዝቃዛም መልካምም ያልኾነ፡፡
Verse 45
ﯪﯫﯬﯭﯮ
ﯯ
እነርሱ ከዚህ በፊት ቅምጥሎች ነበሩና፡፡
Verse 46
ﯰﯱﯲﯳﯴ
ﯵ
በታላቅ ኀጢአትም ላይ ይዘወትሩ ነበሩና፡፡
Verse 47
ይሉም ነበሩ፡- «በሞትንና ዐፈር፣ ዐጥንቶችም በኾን ጊዜ እኛ በእርግጥ የምንቀሰቀስ ነን?
Verse 48
ﰀﰁ
ﰂ
«የፊተኞቹ አባቶቻችንም?»
Verse 49
ﰃﰄﰅﰆ
ﰇ
በላቸው፡- «ፊተኞቹም ኋለኞቹም፡፡
Verse 50
ﰈﰉﰊﰋﰌ
ﰍ
«በተወሰነ ቀን ቀጠሮ በእርግጥ ተሰብሳቢዎች ናቸው፡፡
Verse 51
ﭑﭒﭓﭔﭕ
ﭖ
«ከዚያም እናንተ ጠማሞች አስተባባዮች ሆይ!
Verse 52
ﭗﭘﭙﭚﭛ
ﭜ
« ከዘቁም ዛፍ በእርግጥ በይዎች ናችሁ፡፡
Verse 53
ﭝﭞﭟ
ﭠ
«ከእርሷም ሆዶቻችሁን ሞይዎች ናችሁ፡፡
Verse 54
ﭡﭢﭣﭤ
ﭥ
«በእርሱ ላይም ከፈላ ውሃ ጠጪዎች ናችሁ፡፡
Verse 55
ﭦﭧﭨ
ﭩ
«የተጠሙንም ግመሎች አጠጣጥ ብጤ ጠጪዎች ናችሁ፡፡»
Verse 56
ﭪﭫﭬﭭ
ﭮ
ይህ በፍርዱ ቀን መስተንግዷቸው ነው፡፡
Verse 57
ﭯﭰﭱﭲ
ﭳ
እኛ ፈጠርናችሁ አታምኑምን?
Verse 58
ﭴﭵﭶ
ﭷ
(በማኅፀኖች) የምታፈሱትን አያችሁን?
Verse 59
ﭸﭹﭺﭻﭼ
ﭽ
እናንተ ትፈጥሩታላችሁን? ወይስ እኛ ፈጣሪዎቹን ነን?
Verse 60
እኛ ሞትን (ጊዜውን) በመካከላችሁ ወሰንን፡፡ እኛም ተሸናፊዎች አይደለንም፡፡
Verse 61
ብጤዎቻችሁን በመለወጥና በዚያ በማታውቁትም (ቅርጽ) እናንተን በመፍጠር ላይ (አንሸነፍም)፡፡
Verse 62
ﮐﮑﮒﮓﮔﮕ
ﮖ
የፊተኛይቱንም አፈጣጠር በእርግጥ ዐውቃችኋል፡፡ አትገነዘቡምን?
Verse 63
ﮗﮘﮙ
ﮚ
የምትዘሩትንም አያችሁን?
Verse 64
ﮛﮜﮝﮞﮟ
ﮠ
እናንተ ታበቅሉታላችሁን? ወይስ እኛ አብቃዮቹ ነን?
Verse 65
ﮡﮢﮣﮤﮥﮦ
ﮧ
ብነሻ ኖሮ ደረቅ ስብርብር ባደረግነውና የምትደነቁም በኾናችሁ ነበር፡፡
Verse 66
ﮨﮩ
ﮪ
«እኛ በዕዳ ተያዦች ነን፡፡
Verse 67
ﮫﮬﮭ
ﮮ
«በእርግጥም እኛ (ከመጠቀም) የተከለከልን ነን» (ትሉ ነበር)፡፡
Verse 68
ﮯﮰﮱﯓ
ﯔ
ያንንም የምትጠጡትን ውሃ አየችሁን?
Verse 69
እናንተ ከደመናው አወረዳችሁትን? ወይስ እኛ አውራጆቹ ነን?
Verse 70
ﯝﯞﯟﯠﯡﯢ
ﯣ
ብንሻ ኖሮ መርጋጋ ባደረግነው ነበር፡፡ አታመሰግኑምን?
Verse 71
ﯤﯥﯦﯧ
ﯨ
ያቺንም የምትሰብቋትን እሳት አያችሁን?
Verse 72
ﯩﯪﯫﯬﯭﯮ
ﯯ
እናንተ ዛፏን ፈጠራችሁን? ወይስ እኛ ፈጣሪዎችዋ ነን?
Verse 73
ﯰﯱﯲﯳﯴ
ﯵ
እኛ (ለገሀናም) ማስታወሻ ለመንገደኞችም መጠቀሚያ አደረግናት፡፡
Verse 74
ﯶﯷﯸﯹ
ﯺ
የታላቁን ጌታህንም ስም አወድስ፡፡
Verse 75
ﯻﯼﯽﯾﯿ
ﰀ
በከዋክብትም መጥለቂያዎች እምላለሁ፡፡
Verse 76
ﰁﰂﰃﰄﰅ
ﰆ
እርሱም ብታወቁ ታላቅ መሓላ ነው፡፡
Verse 77
ﭑﭒﭓ
ﭔ
እርሱ የከበረ ቁርኣን ነው፡፡
Verse 78
ﭕﭖﭗ
ﭘ
በተጠበቀ መጽሐፍ ውስጥ ነው፡፡
Verse 79
ﭙﭚﭛﭜ
ﭝ
የተጥራሩት እንጅ ሌላ አይነካውም፡፡
Verse 80
ﭞﭟﭠﭡ
ﭢ
ከዓለማት ጌታ የተወረደ ነው፡፡
Verse 81
ﭣﭤﭥﭦ
ﭧ
በዚህ ንግግር እናንተ ቸልተኞች ናችሁን?
Verse 82
ﭨﭩﭪﭫ
ﭬ
ሲሳያችሁንም (ዝናምን) እናንተ የምታስተባብሉት ታደርጋላችሁን?
Verse 83
ﭭﭮﭯﭰ
ﭱ
(ነፍስ) ጉረሮንም በደረሰች ጊዜ፡፡
Verse 84
ﭲﭳﭴ
ﭵ
እናንተ ያን ጊዜ የምታዩ ስትኾኑ፡፡
Verse 85
እኛም ግን አታዩም እንጅ ከእናንተ ይልቅ ወደእርሱ የቀረብን ስንኾን፡፡
Verse 86
ﭾﭿﮀﮁﮂ
ﮃ
የማትዳኙም ከኾናችሁ፡፡
Verse 87
ﮄﮅﮆﮇ
ﮈ
እውነተኞች እንደ ኾናችሁ (ነፍሲቱን ወደ አካሉ) ለምን አትመልሷትም፡፡
Verse 88
ﮉﮊﮋﮌﮍ
ﮎ
(ሟቹ) ከባለሟሎቹ ቢኾንማ፡፡
Verse 89
ﮏﮐﮑﮒ
ﮓ
(ለእርሱ) ዕረፍት፣ መልካም ሲሳይም፣ የመጠቀሚያ ገነትም አልለው፡፡
Verse 90
ﮔﮕﮖﮗﮘﮙ
ﮚ
ከቀኝ ጓዶችም ቢኾንማ፡፡
Verse 91
ﮛﮜﮝﮞﮟ
ﮠ
ከቀኝ ጓዶች ስለ ኾንክ ላንተ ሰላም አልለህ (ይባላል)፡፡
Verse 92
ﮡﮢﮣﮤﮥﮦ
ﮧ
ከሚያስዋሹት ጠማማዎችም ቢኾንማ፡፡
Verse 93
ﮨﮩﮪ
ﮫ
ከፈላ ውሃ የኾነ መስተንግዶ አልለው፡፡
Verse 94
ﮬﮭ
ﮮ
በገሀነም መቃጠልም (አልለው)፡፡
Verse 95
ﮯﮰﮱﯓﯔ
ﯕ
ይህ እርሱ እርግጠኛ እውነት ነው፡፡
Verse 96
ﯖﯗﯘﯙ
ﯚ
የታላቁንም ጌታህን ስም አወድስ፡፡
تقدم القراءة