የሱራ الشعراء ትርጉም በالأمهرية ከالترجمة الأمهرية
Verse 1
ﭑ
ﭒ
ጠ.ሰ.መ. (ጧ ሲን ሚም)፡፡
Verse 2
ﭓﭔﭕﭖ
ﭗ
ይህች ግልጽ ከኾነው መጽሐፍ አንቀጾች ናት፡፡
Verse 3
ﭘﭙﭚﭛﭜﭝ
ﭞ
አማኞች ባለመኾናቸው፤ (በቁጭት) ነፍስህን ገዳይ መኾን ይፈራልሃል፡፡
Verse 4
ብንሻ በእነሱ ላይ ከሰማይ ተዓምረን እናወርድና አንገቶቻቸው (መሪዎቻቸው) ለእርሷ ተዋራጆች ይኾናሉ፡፡
Verse 5
ከአልረሕማንም ዘንድ ኣዲስ የተወረደ ቁርኣን አይመጣላቸውም፤ ከእርሱ የሚሸሹ ቢኾኑ እንጂ፡፡
Verse 6
በእርግጥም አስተባበሉ፡፡ የዚያም በእርሱ ይሳለቁበት የነበሩት ወሬዎች (ፍጻሜ) ይመጣባቸዋል፡፡
Verse 7
ወደ ምድርም በውስጧ ከመልካም (በቃይ) ጎሳ ሁሉ ብዙን እንዳበቀልን አላዩምን፡፡
Verse 8
በዚህ አስደናቂ ምልክት አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም አማኞች አልነበሩም፡፡
Verse 9
ﮖﮗﮘﮙﮚ
ﮛ
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊ አዛኝ ነው፡፡
Verse 10
ጌታህም ሙሳን «ወደ በደለኞቹ ሕዝቦች ኺድ» በማለት በጠራው ጊዜ (አስታውስ)፡፡
Verse 11
ﮥﮦﮧﮨﮩ
ﮪ
«ወደ ፈርዖን ሕዝቦች (ኺድ) አላህን አይፈሩምን» (አለው)፡፡
Verse 12
ﮫﮬﮭﮮﮯﮰ
ﮱ
(ሙሳም) አለ «ጌታዬ ሆይ! እኔ ሊያስተባብሉኝ እፈራለሁ፡፡
Verse 13
«ልቤም ይጠብባል፡፡ ምላሴም አይፈታም፡፡ ስለዚህ ወደ ሃሩን ላክ፡፡
Verse 14
ﯜﯝﯞﯟﯠﯡ
ﯢ
«ለእነርሱም በእኔ ላይ (የደም) ወንጀል አልለ፡፡ ስለዚህ እንዳይገድሉኝ እፈራለሁ፡፡»
Verse 15
(አላህ) አለ «ተው! (አይነኩህም)፡፡ በተዓምራቶቻችንም ኺዱ፡፡ እኛ ከእናንተ ጋር ሰሚዎች ነንና፡፡
Verse 16
«ወደ ፈርዖንም ኺዱ፡፡ በሉትም፡- እኛ የዓለማት ጌታ መልክተኞች ነን፡፡
Verse 17
ﯵﯶﯷﯸﯹ
ﯺ
«የእስራኤልን ልጆች ከእኛ ጋር ልቀቅ፡፡»
Verse 18
(ፈርዖንም) አለ «ልጅ ኾነህ በእኛ ውስጥ አላሳደግንህምን በእኛ ውስጥም ከዕድሜህ ብዙ ዓመታትን አልተቀመጥክምን
Verse 19
«ያችንም የሠራሃትን ሥራህን አልሠራህምን አንተም ከውለታ ቢሶቹ ነህ» (አለ)፡፡
Verse 20
ﭑﭒﭓﭔﭕﭖ
ﭗ
(ሙሳም) አለ «ያን ጊዜ እኔም ከተሳሳቱት ኾኜ ሠራኋት፡፡
Verse 21
«በፈራኋችሁም ጊዜ ከእንናተ ሸሸሁ፡፡ ጌታየም ለእኔ ጥበብን ሰጠኝ፡፡ ከመልክተኞቹም አደረገኝ፡፡
Verse 22
«ይህችም የእስራኤልን ልጆች ባሪያ በማድረግህ በእኔ ላይ የምትመጻደቅባት ጸጋ ነት፡፡»
Verse 23
ﭭﭮﭯﭰﭱ
ﭲ
ፈርዖን አለ «(ላከኝ የምትለው) የዓለማትም ጌታ ምንድነው»
Verse 24
(ሙሳ) «የሰማያትና የምድር በመካከላቸውም ያለው ሁሉ ጌታ ነው፡፡ የምታረጋግጡ ብትኾኑ (ነገሩ ይህ ነው)፤» አለው፡፡
Verse 25
ﭾﭿﮀﮁﮂ
ﮃ
(ፈርዖንም) በዙሪያው ላሉት ሰዎች «አትሰሙምን» አለ፡፡
Verse 26
ﮄﮅﮆﮇﮈ
ﮉ
(ሙሳ) «ጌታችሁና የመጀመሪያዎቹ አባቶቻችሁም ጌታ ነው» አለው፡፡
Verse 27
(ፈርዖን)
Verse 28
(ሙሳ) «የምሥራቅና የምዕራብ በመካከላቸውም ያለው ነገር ሁሉ ጌታ ነው፡፡ ታውቁ እንደኾናችሁ (እመኑበት)» አለው፡፡
Verse 29
(ፈርዖን) «ከእኔ ሌላ አምላክን ብትይዝ በውነቱ ከእስረኞቹ አደርግሃለሁ» አለ፡፡
Verse 30
ﮦﮧﮨﮩﮪ
ﮫ
(ሙሳ) «በግልጽ አስረጅ ብመጣህም እንኳ» አለው፡፡
Verse 31
«እንግዲያውስ ከእውነተኞች እንደኾንክ (አስረጁን) አምጣው» አለ፡፡
Verse 32
ﯕﯖﯗﯘﯙﯚ
ﯛ
በትሩንም ጣለ፡፡ እርሷም ወዲያውኑ ግልጽ እባብ ኾነች፡፡
Verse 33
ﯜﯝﯞﯟﯠﯡ
ﯢ
እጁንም አወጣ፡፡ ወዲያውም እርሷ ለተመልካቾች (የምታበራ) ነጭ ኾነች፡፡
Verse 34
(ፈርዖን) በዙሪያው ላሉት መማክርት «ይህ በእርግጥ ዐዋቂ ድግምተኛ ነው» አለ፡፡
Verse 35
«ከምድራችሁ በድግምቱ ሊያወጣችሁ ይፈልጋልና ምንን ታዛላችሁ» (አላቸው)፡፡
Verse 36
አሉት «እርሱን ወንድሙንም አቆይና በየከተሞቹ ሰብሳቢዎችን ላክ፡፡
Verse 37
ﯼﯽﯾﯿ
ﰀ
«በጣም ዐዋቂ ድግምተኞችን ሁሉ ያመጡልሃልና፡፡»
Verse 38
ﰁﰂﰃﰄﰅ
ﰆ
ድግምተኞቹም በታወቀ ቀን ቀጠሮ ተሰበሰቡ፡፡
Verse 39
ﰇﰈﰉﰊﰋ
ﰌ
ለሰዎቹም «እናንተ ተሰብስባችኋልን» ተባለ፡፡
Verse 40
«ድግምተኞቹን እነሱ አሸናፊዎች ቢኾኑ እንከተል ዘንድ» (ተባለ)፡፡
Verse 41
«ድግምተኞቹም በመጡ ጊዜ ለፈርዖን እኛ አሸናፊዎች ብንሆን ለእኛ በእርግጥ ዋጋ አለን» አሉት፡፡
Verse 42
ﭦﭧﭨﭩﭪﭫ
ﭬ
«አዎን፤ እናንተም ያን ጊዜ ከባለሟሎቹ ትኾናላችሁ» አላቸው፡፡
Verse 43
ሙሳ «ለእነርሱ እናንተ የምትጥሉትን ጣሉ» አላቸው፡፡
Verse 44
ገመዶቻቸውንና በትሮቻቸውንም ጣሉ፡፡ «በፈርዖንም ክብር ይኹንብን፡፡ እኛ በእርግጥ አሸናፊዎቹ እኛ ነን» አሉ፡፡
Verse 45
ሙሳም በትሩን ጣለ፡፡ ወዲያውም እርሷ የሚያስመስሉትን ሁሉ ትውጣለች፡፡
Verse 46
ﮈﮉﮊ
ﮋ
ድግምተኞቹም ሰጋጆች ኾነው ወደቁ፡፡
Verse 47
ﮌﮍﮎﮏ
ﮐ
(እነሱም) አሉ «በዓለማት ጌታ አመንን፡፡
Verse 48
ﮑﮒﮓ
ﮔ
«በሙሳና በሃሩን ጌታ፡፡»
Verse 49
(ፈርዖንም) «ለእናንተ ሳልፈቅድላችሁ በፊት ለእርሱ አመናችሁን እርሱ ያ ድግምትን ያስተማራችሁ ታላቃችሁ ነው፡፡ ወደፊትም (የሚያገኛችሁን) በእርግጥ ታውቃላችሁ፡፡ እጆቻችሁንና እግሮቻችሁን (ቀኝና ግራን) በማናጋት እቆረርጣለሁ፡፡ ሁላችሁንም እሰቅላችኋለሁም» አለ፡፡
Verse 50
(እነርሱም) አሉ «ጉዳት የለብንም፡፡ እኛ ወደ ጌታችን ተመላሾች ነን፡፡
Verse 51
«እኛ የምእምናን መጀመሪያ በመኾናችን ጌታችን ኀጢአቶቻችንን ለእኛ ሊምር እንከጅላለን፡፡»
Verse 52
ወደ ሙሳም «ባሮቼን ይዘህ ሌሊት ኺድ፡፡ እናንተ የሚከተሉዋችሁ ናችሁና» ስንል ላክን፡፡
Verse 53
ﯭﯮﯯﯰﯱ
ﯲ
ፈርዖንም በየከተሞቹ ሰብሳቢዎችን (እንዲህ ሲል) ላከ፡፡
Verse 54
ﯳﯴﯵﯶ
ﯷ
«እነዚህ ጥቂቶች ጭፈሮች ናቸው፡፡
Verse 55
ﯸﯹﯺ
ﯻ
«እነርሱም ለእኛ አስቆጪዎች ናቸው፡፡
Verse 56
ﯼﯽﯾ
ﯿ
«እኛም ብዙዎች ጥንቁቆች ነን፤» (አለ)፡፡
Verse 57
ﰀﰁﰂﰃ
ﰄ
አወጣናቸውም፡፡ ከአትክልቶችና ከምንጮች፡፡
Verse 58
ﰅﰆﰇ
ﰈ
ከድልቦችም ከመልካም መቀመጫዎችም፡፡
Verse 59
ﰉﰊﰋﰌﰍ
ﰎ
እንደዚሁ ለእስራኤል ልጆች አወረስናትም፡፡
Verse 60
ﰏﰐ
ﰑ
ፀሐይዋ ስትወጣም ተከተሉዋቸው፡፡
Verse 61
ሁለቱ ጭፍሮችም በተያዩ ጊዜ የሙሳ ጓዶች «እኛ(የፈርዖን ሰዎች) የሚደርሱብን ነን» አሉ፡፡
Verse 62
(ሙሳ) «ተዉዉ! ጌታዬ ከእኔ ጋር ነው፡፡ በእርግጥ ይመራኛል» አለ፡፡
Verse 63
ወደ ሙሳም «ባሕሩን በበትርህ ምታው» ስንል ላክንበት፡፡ (መታውና) ተከፈለም፡፡ ክፍሉም ሁሉ እንደ ታላቅ ጋራ ኾነ፡፡
Verse 64
ﭱﭲﭳ
ﭴ
እዚያም ዘንድ ሌሎችን አቀረብን፡፡
Verse 65
ﭵﭶﭷﭸﭹ
ﭺ
ሙሳንም ከእርሱ ገር ያሉትንም ሰዎች ሁሉንም አዳን፡፡
Verse 66
ﭻﭼﭽ
ﭾ
ከዚያም ሌሎቹን አሰጠምን፡፡
Verse 67
በዚህ ውስጥ ታላቅ ታምር አለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም አማኞች አልነበሩም፡፡
Verse 68
ﮉﮊﮋﮌﮍ
ﮎ
ጌታህም እርሱ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
Verse 69
ﮏﮐﮑﮒ
ﮓ
በእነሱም (በሕዝቦችህ) ላይ የኢብራሂምን ወሬ አንብብላቸው፡፡
Verse 70
ﮔﮕﮖﮗﮘﮙ
ﮚ
ለአባቱና ለሕዝቦቹ «ምንን ትግገዛላችሁ» ባለ ጊዜ፡፡
Verse 71
ﮛﮜﮝﮞﮟﮠ
ﮡ
«ጣዖታትን እንገዛለን፤ እርሷንም በመገዛት ላይ እንቆያለን» አሉ፡፡
Verse 72
ﮢﮣﮤﮥﮦ
ﮧ
(እርሱም) አለ «በጠራችኋቸው ጊዜ ይሰሟችኋልን
Verse 73
ﮨﮩﮪﮫ
ﮬ
«ወይስ ይጠቅሟችኋልን ወይስ ይጎዷችኋልን»
Verse 74
ﮭﮮﮯﮰﮱﯓ
ﯔ
«የለም! አባቶቻችን እንደዚሁ ሲሠሩ አገኘን» አሉት፡፡
Verse 75
ﯕﯖﯗﯘﯙ
ﯚ
«ትግገዙት የነበራችሁትን አስተዋላችሁን
Verse 76
ﯛﯜﯝ
ﯞ
«እናንተም የቀድሞዎቹ አባቶቻችሁም (የተግገዛችሁትን)፡፡»
Verse 77
ﯟﯠﯡﯢﯣﯤ
ﯥ
«እነሱም (ጣዖቶቹ) ለእኔ ጠላቶች ናቸው፡፡ ግን የዓለማት ጌታ ሲቀር (እርሱ ወዳጄ ነው)፡፡
Verse 78
ﯦﯧﯨﯩ
ﯪ
«(እርሱ) ያ የፈጠረኝ ነው፡፡ እርሱም ይመራኛል፡፡
Verse 79
ﯫﯬﯭﯮ
ﯯ
«ያም እርሱ የሚያበላኝና የሚያጠጣኝ ነው፡፡
Verse 80
ﯰﯱﯲﯳ
ﯴ
«በታመምኩም ጊዜ እርሱ ያሽረኛል፡፡
Verse 81
ﯵﯶﯷﯸ
ﯹ
«ያም የሚገድለኝ ከዚያም ሕያው የሚያደርገኝ ነው፡፡
Verse 82
ያም በፍርዱ ቀን ኀጢአቴን ለእኔ ሊምር የምከጅለው ነው፡፡
Verse 83
ﰃﰄﰅﰆﰇﰈ
ﰉ
ጌታዬ ሆይ! ዕውቀትን ስጠኝ! በደጋጎቹም ሰዎች አስጠጋኝ፡፡
Verse 84
ﭑﭒﭓﭔﭕﭖ
ﭗ
በኋለኞቹም ሕዝቦች ውስጥ ለእኔ መልካም ዝናን አድርግልኝ፡፡
Verse 85
ﭘﭙﭚﭛﭜ
ﭝ
የጸጋይቱን ገነት ከሚወርሱትም አድርገኝ፡፡
Verse 86
ﭞﭟﭠﭡﭢﭣ
ﭤ
ለአባቴም ማር፡፡ እርሱ ከተሳሳቱት ነበረና፡፡
Verse 87
ﭥﭦﭧﭨ
ﭩ
በሚቀሰቀሱበት ቀንም አታዋርደኝ፡፡
Verse 88
ﭪﭫﭬﭭﭮﭯ
ﭰ
ገንዘብም ልጆችም በማይጠቅሙበት ቀን፡፡
Verse 89
ﭱﭲﭳﭴﭵﭶ
ﭷ
ወደ አላህ በንጹህ ልብ የመጣ ሰው ቢኾን እንጅ፡፡»
Verse 90
ﭸﭹﭺ
ﭻ
ገነትም ለፈሪዎች በምትቀረብበት (ቀን)፡፡
Verse 91
ﭼﭽﭾ
ﭿ
ገሀነምም ለጠመሞች በምትገለጽበት (ቀን)፡፡
Verse 92
ﮀﮁﮂﮃﮄﮅ
ﮆ
ለእነሱም በሚባል ቀን «ትግገዟቸው የነበራችሁት የት ናቸው»
Verse 93
«ከአላህ ሌላ ሲኾኑ ይረዱዋችኋልን ወይስ (ለራሳቸው) ይርረዳሉን»
Verse 94
ﮏﮐﮑﮒ
ﮓ
በውስጧም እነሱና ጠማሞቹ በፊቶቻቸው ተጥለው ይንከባለላሉ፡፡
Verse 95
ﮔﮕﮖ
ﮗ
የሰይጣንም ሰራዊቶች መላውም (ይጣላሉ)፡፡
Verse 96
ﮘﮙﮚﮛ
ﮜ
እነርሱም በእርሷ ውስጥ የሚከራከሩ ኾነው ይላሉ፡-
Verse 97
ﮝﮞﮟﮠﮡﮢ
ﮣ
በአላህ እንምላለን፤ እኛ በግልጽ መሳሳት ውስጥ ነበርን፡፡
Verse 98
ﮤﮥﮦﮧ
ﮨ
(ጣዖቶቹን) በዓለማት ጌታ ባስተካከልናችሁ ጊዜ፡፡
Verse 99
ﮩﮪﮫﮬ
ﮭ
አመጸኞቹም እንጅ ሌላ አላሳሳተንም፡፡
Verse 100
ﮮﮯﮰﮱ
ﯓ
ከአማላጆችም ለእኛ ምንም የለንም፡፡
Verse 101
ﯔﯕﯖ
ﯗ
አዛኝ ወዳጂም (የለንም)፡፡
Verse 102
ለእኛም አንዲት ጊዜ መመለስ በኖረችንና ከአማኞቹ በኾን እንመኛለን (ይላሉ)፡፡
Verse 103
በዚህ ውስጥ አስደናቂ ግሳጼ አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም አማኞች አልነበሩም፡፡
Verse 104
ﯪﯫﯬﯭﯮ
ﯯ
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
Verse 105
ﯰﯱﯲﯳ
ﯴ
የኑሕ ሕዝቦች መልክተኞችን አስተባበሉ፡፡
Verse 106
ወንድማቸው ኑሕ ለእነሱ ባላቸው ጊዜ «አትጠነቀቁምን
Verse 107
ﯽﯾﯿﰀ
ﰁ
«እኔ ለእናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡
Verse 108
ﰂﰃﰄ
ﰅ
«አላህንም ፍሩ ታዘዙኝም፡፡
Verse 109
«በእርሱም ላይ ምንም ዋጋ አልጠይቃችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡
Verse 110
ﰓﰔﰕ
ﰖ
«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡»
Verse 111
ﰗﰘﰙﰚﰛﰜ
ﰝ
(እነርሱም) «ወራዶቹ የተከተሉህ ኾነህ ለአንተ እናምናለን» አሉት፡፡
Verse 112
ﭑﭒﭓﭔﭕﭖ
ﭗ
(እርሱም) አላቸው «ይሠሩት በነበሩት ነገር ምን ዕውቀት አለኝ፡፡
Verse 113
«ምርመራቸው በጌታዬ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡ ብታውቁ ኖሮ (ይህንን ትርረዱ ነበር)፡፡
Verse 114
ﭡﭢﭣﭤ
ﭥ
«እኔም አማኞችን አባራሪ አይደለሁም፡፡
Verse 115
ﭦﭧﭨﭩﭪ
ﭫ
«እኔ ግልጽ አስፈራሪ እንጅ ሌላ አይደለሁም፡፡»
Verse 116
«ኑሕ ሆይ! (ከምትለው) ባትከለከል በእርግጥ ከሚወገሩት ትኾናለህ» አሉት፡፡
Verse 117
ﭵﭶﭷﭸﭹ
ﭺ
(እርሱም) አለ «ጌታዬ ሆይ! ሕዝቦቼ አስተባበሉኝ፡፡
Verse 118
«በእኔና በእነርሱም መካከል (ተገቢ) ፍርድን ፍረድ፡፡ አድነኝም፡፡ ከእኔ ጋር ያሉትንም ምእምናን፡፡»
Verse 119
ﮅﮆﮇﮈﮉﮊ
ﮋ
እርሱንም ከእርሱ ጋር ያለውንም ሁሉ በተመላው መርከብ ውስጥ አዳን፡፡
Verse 120
ﮌﮍﮎﮏ
ﮐ
ከዚያም በኋላ ቀሪዎቹን አሰጠምን፡፡
Verse 121
በዚህ ውስጥ ታላቅ ግሳጼ አለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም አማኞች አልነበሩም፡፡
Verse 122
ﮛﮜﮝﮞﮟ
ﮠ
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
Verse 123
ﮡﮢﮣ
ﮤ
ዓድ መልክተኞችን አስተባበለች፡፡
Verse 124
ወንድማቸው ሁድ ለነርሱ ባላቸው ጊዜ «አትጠነቀቁምን
Verse 125
ﮭﮮﮯﮰ
ﮱ
«እኔ ለናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡
Verse 126
ﯓﯔﯕ
ﯖ
«አላህንም ፍሩ ታዘዙኝም፡፡
Verse 127
«በእርሱም ላይ ምንም ዋጋ አለምናችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡
Verse 128
ﯤﯥﯦﯧﯨ
ﯩ
«የምትጫወቱ ኾናችሁ በከፍተኛ ስፍራ ሁሉ ላይ ምልክትን ትገነባላችሁን
Verse 129
ﯪﯫﯬﯭ
ﯮ
«የውሃ ማጠራቀሚያዎችንና ሕንፃዎችንም ዘላለም መኖርን የምትከጅሉ ኾናችሁ ትሠራላችሁን
Verse 130
ﯯﯰﯱﯲ
ﯳ
«በቀጣችሁም ጊዜ ጨካኞች ኾናችሁ ትቀጣላችሁን
Verse 131
ﯴﯵﯶ
ﯷ
«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡
Verse 132
ﯸﯹﯺﯻﯼ
ﯽ
«ያንንም በምታውቁት (ጸጋ) ያጣቀማችሁን ፍሩ፡፡
Verse 133
ﯾﯿﰀ
ﰁ
«በእንስሳዎችና በልጆች ያጣቀማችሁን፡፡
Verse 134
ﰂﰃ
ﰄ
«በአትክልቶችና በምንጮችም፡፡
Verse 135
ﰅﰆﰇﰈﰉﰊ
ﰋ
«እኔ በእናንተ ላይ የታላቅን ቀን ቅጣት እፈራለሁና፡፡»
Verse 136
(እነርሱም) አሉ «ብትገስጽም ወይም ከገሳጮቹ ባትኾንም በእኛ ላይ እኩል ነው፤ (ያለንበትን አንለቅም)፡፡
Verse 137
ﭑﭒﭓﭔﭕ
ﭖ
«ይህ የፊተኞቹ ሰዎች ፀባይ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡
Verse 138
ﭗﭘﭙ
ﭚ
«እኛም የምንቅቀጣ አይደለንም» (አሉ)፡፡
Verse 139
አስተባበሉትም፡፡ አጠፋናቸውም፡፡ በዚህም ውስጥ እርግጠኛ ግሳጼ አለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም ምእመናን አልነበሩም፡፡
Verse 140
ﭨﭩﭪﭫﭬ
ﭭ
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
Verse 141
ﭮﭯﭰ
ﭱ
ሰሙድ መልክተኞችን አስተባበለች፡፡
Verse 142
ወንድማቸው ሷሊህ ለእነርሱ ባላቸው ጊዜ «አትጠነቀቁምን
Verse 143
ﭺﭻﭼﭽ
ﭾ
«እኔ ለእናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡
Verse 144
ﭿﮀﮁ
ﮂ
«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡
Verse 145
«በእርሱም ላይ ምንም ዋጋ አልለምናችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡
Verse 146
ﮐﮑﮒﮓﮔ
ﮕ
«በዚያ እዚህ ባለው (ጸጋ) ውስጥ የረካችሁ ኾናችሁ ትተዋላችሁን
Verse 147
ﮖﮗﮘ
ﮙ
«በአትክልቶችና በምንጮች ውስጥ፡፡
Verse 148
ﮚﮛﮜﮝ
ﮞ
«በአዝመራዎችም ፍሬዋ የበሰለ በኾነች ዘንባባም፤ (ውስጥ ትተዋላችሁን)
Verse 149
ﮟﮠﮡﮢﮣ
ﮤ
«ብልሆች ኾናችሁ ከጋራዎች ቤቶችንም ትጠርባላችሁ፡፡
Verse 150
ﮥﮦﮧ
ﮨ
«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡
Verse 151
ﮩﮪﮫﮬ
ﮭ
«የወሰን አላፊዎችንም ትዕዛዝ አትከተሉ፡፡
Verse 152
ﮮﮯﮰﮱﯓﯔ
ﯕ
«የእነዚያን በምድር ላይ የሚያጠፉትንና የማያበጁትን፡፡»
Verse 153
ﯖﯗﯘﯙﯚ
ﯛ
(እነሱም) አሉ «አንተ በብዙ ከተደገመባቸው ሰዎች ብቻ ነህ፡፡
Verse 154
«አንተ ብጤያችን ሰው እንጅ ሌላ አይደለህም፡፡ ከእውነተኞቹም እንደኾንክ ተዓምርን አምጣ፡፡»
Verse 155
(እርሱም) አለ «ይህች ግመል ናት፡፡ ለእርሷ የመጠጥ ፋንታ አላት፡፡ ለእናንተም የታወቀ ቀን ፋንታ አላችሁ፡፡
Verse 156
«በክፉም አትንኳት፡፡ የታላቅ ቀን ቅጣት ይይዛችኋልና፡፡»
Verse 157
ﯺﯻﯼ
ﯽ
ወጓትም፡፡ ወዲያውም ተጸጻቾች ኾነው አነጉ፡፡
Verse 158
ቅጣቱም ያዛቸው፡፡ በዚህም ውስጥ ግሳፄ አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም ምእመናን አልነበሩም፡፡
Verse 159
ﰋﰌﰍﰎﰏ
ﰐ
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
Verse 160
ﭑﭒﭓﭔ
ﭕ
የሉጥ ሕዝቦች መልክተኞችን አስተባባሉ፡፡
Verse 161
ወንድማቸው ሉጥ ለእነርሱ ባለ ጊዜ «አትጠነቀቁምን
Verse 162
ﭞﭟﭠﭡ
ﭢ
«እኔ ለእናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡
Verse 163
ﭣﭤﭥ
ﭦ
«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡
Verse 164
«በእርሱም ላይ ምንም ዋጋ አልለምናችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡
Verse 165
ﭴﭵﭶﭷ
ﭸ
«ከዓለማት ሰዎች ወንዶችን ትመጣላችሁን
Verse 166
«ከሚስቶቻችሁም ጌታችሁ ለናንተ የፈጠረላችሁን ትተዋላችሁን በእውነቱ እናንተ ወሰን አላፊዎች ሕዝቦ ናችሁ፡፡»
Verse 167
(እነርሱም) አሉ «ሉጥ ሆይ! ባትከለከል በእርግጥ (ከአገር) ከሚወጡት ትኾናለህ፡፡»
Verse 168
ﮏﮐﮑﮒﮓ
ﮔ
(እርሱም) አለ «እኔ ሥራችሁን ከሚጠሉት ሰዎች ነኝ፡፡
Verse 169
ﮕﮖﮗﮘﮙ
ﮚ
«ጌታዬ ሆይ! እኔንም ቤተሰቦቼንም ከሚሠሩት ሥራ (ቅጣት) አድነን፡፡»
Verse 170
ﮛﮜﮝ
ﮞ
እርሱንም ቤተሰቦቹንም በጠቅላላ አዳንናቸው፡፡
Verse 171
ﮟﮠﮡﮢ
ﮣ
በቀሪዎቹ ውስጥ የኾነች አሮጊት ብቻ ስትቀር (እርሷ ጠፋች)፡፡
Verse 172
ﮤﮥﮦ
ﮧ
ከዚያም ሌሎቹን አጠፋን፡፡
Verse 173
በእነሱም ላይ (የድንጋይን) ዝናምን አዘነምንባቸው፡፡ የተስፈራሪዎቹም ዝናም (ምንኛ) ከፋ፡፡
Verse 174
በዚህ ውስጥ አስደናቂ ተዓምር አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም ምእመናን አልነበሩም፡፡
Verse 175
ﯛﯜﯝﯞﯟ
ﯠ
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
Verse 176
ﯡﯢﯣﯤ
ﯥ
የአይከት ሰዎች መልክተኞችን አስተባበሉ፤
Verse 177
ﯦﯧﯨﯩﯪﯫ
ﯬ
ሹዕይብ ለእነርሱ ባላቸው ጊዜ «አትጠነቀቁምን
Verse 178
ﯭﯮﯯﯰ
ﯱ
«እኔ ለእናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡
Verse 179
ﯲﯳﯴ
ﯵ
«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡
Verse 180
«በርሱም ላይ ምንም ዋጋ አልጠይቃችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡
Verse 181
«ስፍርን ሙሉ፡፡ ከአጉዳዮቹም አትኹኑ፡፡
Verse 182
ﰋﰌﰍ
ﰎ
«በትክክለኛ ሚዛንም መዝኑ፡፡
Verse 183
«ሰዎችንም ነገሮቻቸውን አታጉድሉባቸው፡፡ በምድርም ላይ አጥፊዎች ኾናችሁ አታበላሹ፡፡
Verse 184
ﭑﭒﭓﭔﭕ
ﭖ
«ያንንም የፈጠራችሁን የቀድሞዎቹንም ፍጡሮች (የፈጠረውን) ፍሩ፡፡»
Verse 185
ﭗﭘﭙﭚﭛ
ﭜ
አሉ «አንተ በብዛት ከተደገመባቸው ሰዎች ነህ፡፡
Verse 186
«አንተም ብጤያችን ሰው እንጅ ሌላ አይደለህም፡፡ እነሆ ከውሸታሞች ነህ ብለን እንጠረጥርሃለን፡፡
Verse 187
«ከእውነተኞቹም እንደኾንክ በእኛ ላይ ከሰማይ ቁራጭን ጣልብን፡፡»
Verse 188
ﭱﭲﭳﭴﭵ
ﭶ
«ጌታዬ የምትሠሩትን ሁሉ ዐዋቂ ነው፤» አላቸው፡፡
Verse 189
አስተባበሉትም፡፡ የጥላይቷ ቀን ቅጣትም ያዛቸው፡፡ እርሱ የከባድ ቀን ቅጣት ነበርና፡፡
Verse 190
በዚህ ውስጥ አስደናቂ ተዓምር አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም ምእምናን አልነበሩም፡፡
Verse 191
ﮍﮎﮏﮐﮑ
ﮒ
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
Verse 192
ﮓﮔﮕﮖ
ﮗ
እርሱም (ቁርኣን) በእርግጥ ከዓለማት ጌታ የተወረደ ነው፡፡
Verse 193
ﮘﮙﮚﮛ
ﮜ
እርሱን ታማኙ መንፈስ (ጂብሪል) አወረደው፤
Verse 194
ﮝﮞﮟﮠﮡ
ﮢ
ከአስፈራሪዎቹ (ነቢያት) ትኾን ዘንድ በልብህ ላይ (አወረደው)፡፡
Verse 195
ﮣﮤﮥ
ﮦ
ግልጽ በኾነ ዐረብኛ ቋንቋ፡፡
Verse 196
ﮧﮨﮩﮪ
ﮫ
እርሱም (ቁርኣን) በቀድሞዎቹ መጻሐፍት ውስጥ (የተወሳ ነው)፡፡
Verse 197
የእስራኤል ልጆች ሊቃውንት የሚያውቁት መኾኑ ለእነርሱ (ለመካ ከሓዲዎች) ምልክት አይኾናቸውምን
Verse 198
ﯗﯘﯙﯚﯛ
ﯜ
ከአዕጀሞች ባንዱ ላይ ባወረድነውም ኖሮ፤
Verse 199
ﯝﯞﯟﯠﯡﯢ
ﯣ
በእነርሱ ላይ ባነበበውም በእርሱ አማኞች አይኾኑም ነበር፡፡
Verse 200
ﯤﯥﯦﯧﯨ
ﯩ
እንደዚሁ (ማስተባበልን) በተንኮለኞች ልቦች ውስጥ አስገባነው፡፡
Verse 201
አሳማሚ ቅጣትን እስከሚያዩ ድረስ በእርሱ አያምኑም፡፡
Verse 202
ﯲﯳﯴﯵﯶ
ﯷ
እነርሱ የማያውቁ ሲኾኑ (ቅጣቱ) ድንገት እስከሚመጣባቸውም ድረስ (አያምኑም)፡፡
Verse 203
ﯸﯹﯺﯻ
ﯼ
(በመጣባቸው ጊዜ) «እኛ የምንቆይ ነን» እስከሚሉም (አያምኑም)፡፡
Verse 204
ﯽﯾ
ﯿ
በቅጣታችን ያቻኩላሉን
Verse 205
ﰀﰁﰂﰃ
ﰄ
አየህን ብዙ ዓመታትን ብናጣቅማቸው፤
Verse 206
ﰅﰆﰇﰈﰉ
ﰊ
ከዚያም ያ ይስፈራሩበት የነበሩት ቢመጣባቸው፤
Verse 207
ﭑﭒﭓﭔﭕﭖ
ﭗ
ይጣቀሙበት የነበሩት ሁሉ ከእነሱ ምንም አያብቃቃቸውም፡፡
Verse 208
አንዲትንም ከተማ ለእርሷ አስፈራሪዎች ያሏት (እና ያስተባበለች) ኾና እንጅ አላጠፋንም፡፡
Verse 209
ﭠﭡﭢﭣ
ﭤ
(ይህች) ግሳፄ ናት፡፡ በዳዮችም አልነበርንም፡፡
Verse 210
ﭥﭦﭧﭨ
ﭩ
ሰይጣናትም እርሱን (ቁርኣንን) አላወረዱትም፡፡
Verse 211
ﭪﭫﭬﭭﭮ
ﭯ
ለእነርሱም አይገባቸውም፤ አይችሉምም፡፡
Verse 212
ﭰﭱﭲﭳ
ﭴ
እነርሱ (የመላእክትን ንግግር) ከመስማት ተከለከሉ ናቸው፡፡
Verse 213
ከአላህም ጋር ሌላን አምላክ አትግገዛ፤ ከሚቀጡት ትኾናለህና፡፡
Verse 214
ﭿﮀﮁ
ﮂ
ቅርቦች ዘመዶችህንም አስጠንቅቅ፡፡
Verse 215
ﮃﮄﮅﮆﮇﮈ
ﮉ
ከምእምናንም ለተከተሉህ ሰዎች ክንፍህን ዝቅ አድርግ፤ (ልዝብ ኹን)፡፡
Verse 216
«እንቢ» ቢሉህም «እኔ ከምትሠሩት ንጹሕ ነኝ» በላቸው፡፡
Verse 217
ﮒﮓﮔﮕ
ﮖ
አሸናፊ አዛኝ በኾነው (ጌታህ) ላይም ተጠጋ፡፡
Verse 218
ﮗﮘﮙﮚ
ﮛ
በዚያ ለሶላት በምትቆም ጊዜ በሚያይህ፡፡
Verse 219
ﮜﮝﮞ
ﮟ
በሰጋጆች ውስጥ መዘዋወርህንም (በሚያየው ጌታህ ላይ ተጠጋ)፡፡
Verse 220
ﮠﮡﮢﮣ
ﮤ
እነሆ እርሱ ሰሚው ዐዋቂው ነውና፡፡
Verse 221
ﮥﮦﮧﮨﮩﮪ
ﮫ
ሰይጣናት በማን ላይ እንደሚወርዱ ልንገራችሁን
Verse 222
ﮬﮭﮮﮯﮰ
ﮱ
በውሸታም ኀጢአተኛ ሁሉ ላይ ይወርዳሉ፡፡
Verse 223
ﯓﯔﯕﯖ
ﯗ
የሰሙትን (ወደ ጠንቋዮች) ይጥላሉ፡፡ አብዛኞቻቸውም ውሸታሞች ናቸው፡፡
Verse 224
ﯘﯙﯚ
ﯛ
ባለ ቅኔዎችንም ጠማማዎቹ ይከተሉዋቸዋል፡፡
Verse 225
እነርሱ በ(ንግግር) ሸለቆ ሁሉ የሚዋልሉ መኾናቸውን አታይምን
Verse 226
ﯤﯥﯦﯧﯨ
ﯩ
እነሱም የማይሠሩትን ነገር የሚናገሩ መኾናቸውን (አታይምን)፤
Verse 227
እነዚያ ያመኑና መልካም ሥራዎችን የሠሩ አላህንም በብዛት ያወሱ ከተበደሉም በኋላ (በቅኔ) የተከላከሉ ሲቀሩ፤ (እነርሱ አይወቀሱም)፡፡ እነዚያም የበደሉ (ከሞቱ በኋላ) እንዴት ያለን መመለስ እንደሚመለሱ በእርግጥ ያውቃሉ፡፡
تقدم القراءة