የሱራ القلم ትርጉም በالأمهرية ከالترجمة الأمهرية
Verse 1
ﮉﮊﮋﮌﮍ
ﮎ
ነ.(ኑን)፤ በብርእ እምላለሁ በዚያም (መልአኮች) በሚጽፉት፡፡
Verse 2
ﮏﮐﮑﮒﮓ
ﮔ
አንተ በጌታህ ጸጋ የተጎናጸፍክ ስትኾን ዕብድ አይደለህም፡፡
Verse 3
ﮕﮖﮗﮘﮙ
ﮚ
ላንተም (ከጌታህ) የማይቋረጥ ዋጋ በእርግጥ አልለህ፡፡
Verse 4
ﮛﮜﮝﮞ
ﮟ
አንተም በታላቅ ጠባይ ላይ ነህ፡፡
Verse 5
ﮠﮡ
ﮢ
ወደፊትም ታያለህ፤ ያያሉም፡፡
Verse 6
ﮣﮤ
ﮥ
ዕብደት በማንኛችሁ እንዳልለ፡፡
Verse 7
ጌታህ እርሱ ከመንገዱ የተሳሳተውን ሰው ዐዋቂ ነው፡፡ እርሱም ተመሪዎቹን ዐዋቂ ነው፡፡
Verse 8
ﯓﯔﯕ
ﯖ
ለአስተባባዮችም አትታዝዙ፡፡
Verse 9
ﯗﯘﯙﯚ
ﯛ
ብትመሳሰላቸውና ቢመሳሰሉህ ተመኙ፡፡
Verse 10
ﯜﯝﯞﯟﯠ
ﯡ
ወራዳንም ሁሉ አትታዘዝ፡፡
Verse 11
ﯢﯣﯤ
ﯥ
ሰውን አነዋሪንና በማሳበቅ ኼያጅን፡፡
Verse 12
ﯦﯧﯨﯩ
ﯪ
ለበጎ ነገር በጣም ከልካይን፣ ወሰን አላፊን፣ ኃጢአተኛን፤
Verse 13
ﯫﯬﯭﯮ
ﯯ
ልበ ደረቅን፣ ከዚህ በኋላ ዲቃላን (ሁሉ አትታዘዝ)፡፡
Verse 14
ﯰﯱﯲﯳﯴ
ﯵ
የገንዘብና የልጆች ባለቤት በመኾኑ (ያስተባብላል)፡፡
Verse 15
በእርሱ ላይ አንቀጾቻችን በሚነበቡ ጊዜ «የመጀመሪያዎቹ ሰዎች ተረቶች ናቸው» ይላል፡፡
Verse 16
ﯾﯿﰀ
ﰁ
በአፍንጫው ላይ በእርግጥ (የሚነወርበት) ምልክት እናደርግበታለን፡፡
Verse 17
እኛ የአትክልቲቱን ባለቤቶቸ እንደ ሞከርን (የመካን ሰዎች) ሞከርናቸው፡፡ ማልደው (ፍሬዋን) ሊለቅሟት በማሉ ጊዜ፡፡
Verse 18
ﭜﭝ
ﭞ
(በመሓላቸው) አያስቀሩምም፡፡
Verse 19
እነርሱ የተኙ ኾነውም ሳሉ ከጌታህ የኾነ ዟሪ በእርሷ ላይ ዞረባት፡፡
Verse 20
ﭧﭨ
ﭩ
እንደ ሌሊት ጨለማም ኾና አነጋች፤ (ከሰለች)፡፡
Verse 21
ﭪﭫ
ﭬ
ያነጉም ኾነው ተጠራሩ፡፡
Verse 22
«ቆራጮች እንደ ኾናችሁ በእርሻቸሁ ላይ ማልዱ» በማለት፡፡
Verse 23
ﭵﭶﭷ
ﭸ
እነርሱ የሚንሾካሾኩ ኾነው ኼዱም፡፡
Verse 24
ﭹﭺﭻﭼﭽﭾ
ﭿ
ዛሬ በእናንተ ላይ ድኻ እንዳይገባት በማለት፡፡
Verse 25
ﮀﮁﮂﮃ
ﮄ
(ድኾችን) በመከልከልም ላይ (በሐሳባቸው) ቻዮች ኾነው ማለዱ፡፡
Verse 26
ﮅﮆﮇﮈﮉ
ﮊ
(ተቃጥላ) ባዩዋትም ጊዜ «እኛ በእርግጥ ተሳሳቾች ነን» አሉ፡፡
Verse 27
ﮋﮌﮍ
ﮎ
«ይልቁንም እኛ የተከለከልን ነን» አሉ፡፡
Verse 28
ትክክለኛቸው «ለእናንተ አላህን ለምን አታጠሩም አላልኳችሁምን?» አላቸው፡፡
Verse 29
ﮗﮘﮙﮚﮛﮜ
ﮝ
«ጌታችን ጥራት ይገባው፡፡ እኛ በዳዮች ነበርን፤» አሉ፡፡
Verse 30
ﮞﮟﮠﮡﮢ
ﮣ
የሚወቃቀሱም ኾነው ከፊሎቻቸው በከፊሉ ላይ መጡ፡፡
Verse 31
ﮤﮥﮦﮧﮨ
ﮩ
«ዋ ጥፋታችን! እኛ ድንበር አላፊዎች ነበርን፤» አሉ፡፡
Verse 32
«ጌታችን ከእርሷ የተሻለን (አትክልት) ሊለውጠን ይከጀላል፡፡ እኛ ወደ ጌታችን ከጃዮች ነን፤» (አሉ)፡፡
Verse 33
ቅጣቱ እንደዚሁ ነው፡፡ የመጨረሻይቱም ዓለም ቅጣት ታላቅ ነው፡፡ የሚያውቁት በኾኑ ኖሮ (በተጠነቀቁ ነበር)፡፡
Verse 34
ﯡﯢﯣﯤﯥﯦ
ﯧ
ለጥንቁቆቹ በጌታቸው ዘንድ መጠቀሚያ ገነቶች አሏቸው፡፡
Verse 35
ﯨﯩﯪ
ﯫ
ሙስሊሞቹን እንደ ከሓዲዎች እናደርጋለን?
Verse 36
ﯬﯭﯮﯯ
ﯰ
ለእናንተ ምን (አስረጅ) አላችሁ? እንዴት ትፈርዳላችሁ፡፡
Verse 37
ﯱﯲﯳﯴﯵ
ﯶ
በእውነቱ ለእናንተ በእርሱ የምታጠኑበት መጽሐፍ አላችሁን?
Verse 38
ﯷﯸﯹﯺﯻ
ﯼ
በውስጡ ለእናንተ የምትመርጡት አላችሁ (የሚል)
Verse 39
ወይስ ለእናንተ የምትፈርዱት አላችሁ በማለት (ቃል ኪዳን የገባንላችሁ) እስከ ትንሣኤ ቀን ደራሽ የኾኑ መሓላዎች ለእናንተ በእኛ ላይ አሏችሁን?
Verse 40
ﰊﰋﰌﰍ
ﰎ
በዚህ ማንኛቸው ተያያዥ እንደ ኾነ ጠይቃቸው፡፡
Verse 41
ወይስ ለእነርሱ (በፍርዳቸው ተስማሚ) «ተጋሪዎች» አሏቸውን? እውነተኞችም እንደኾኑ «ተጋሪዎቻቸውን» ያምጡ፡፡
Verse 42
ባት የሚገለጥበትን (ከሓዲዎች) ወደ መስገድም የሚጥጠሩበትንና የማይችሉበት ቀን (አስታውስ)፡፡
Verse 43
ዓይኖቻቸው የፈሩ ውርደት የምትሸፍናቸው ሲኾኑ፤ (ወደ ስግደት የሚጠሩበትን)፤ እነርሱም (በምድረ ዓለም) ደህና ኾነው ሳሉ ወደ ስግደት በእርግጥ ይጠሩ ነበሩ፡፡
Verse 44
በዚህም ንግግር ከሚያስተባብሉት ሰዎች ጋር ተዎኝ፡፡ (እነርሱን እኔ እበቃሃለሁ)፡፡ ከማያውቁት ስፍራ አዘናግተን እንይዛቸዋለን፡፡
Verse 45
ﭪﭫﭬﭭﭮﭯ
ﭰ
እነርሱንም አዘገያለሁ፡፡ ዘዴዬ ብርቱ ነውና፡፡
Verse 46
በእውነቱ ዋጋን ትጠይቃቸዋለህን? ስለዚህ እነርሱ ከዕዳ የተከበዱ ናቸውን?
Verse 47
ﭹﭺﭻﭼﭽ
ﭾ
ወይስ እነርሱ ዘንድ የሩቁ ምስጢር ዕውቀት አልለን? ስለዚህ እነርሱ ይጽፋሉን?
Verse 48
ለጌታህም ፍርድ ታገሥ፤ (በመበሳጨትና ባለ መታገሥ) እንደ ዓሣው ባለቤትም (እንደ ዮናስ) አትኹን፡፡ እርሱ በጭንቀት የተመላ ኾኖ (ጌታውን) በተጣራ ጊዜ፡፡
Verse 49
ከጌታው የኾነ ጸጋ ባላገኘው ኖሮ በምድረ በዳ ተወቃሽ ኾኖ በተጣለ ነበር፡፡
Verse 50
ﮖﮗﮘﮙﮚ
ﮛ
ጌታውም (በነቢይነት) መረጠው፡፡ ከደጋጎቹም አደረገው፡፡
Verse 51
እነሆ እነዚያም የካዱት ሰዎች ቁርኣኑን በሰሙ ጊዜ በዓይኖቻቸው ሊጥሉህ (ሊያጠፉህ) ይቀርባሉ፡፡ «እርሱም በእርግጥ ዕብድ ነው» ይላሉ፡፡
Verse 52
ﮩﮪﮫﮬﮭ
ﮮ
ግን እርሱ (ቁርኣን) ለዓለማት መገሰጫ እንጂ ሌላ አይደለም፡፡
تقدم القراءة