سورة المطففين

الترجمة الأمهرية

የሱራ المطفّفين ትርጉም በالأمهرية ከالترجمة الأمهرية

الترجمة الأمهرية

Verse 1
ለሰላቢዎች ወዮላቸው፡፡
ለእነርሱም (ለሰዎቹ) በሰፈሩ ወይም በመዘኑላቸው ጊዜ የሚያጎድሉ (ለኾኑት)፡፡
እነዚያ እነርሱ ተቀስቃሾች መኾናቸውን አያውቁምን?
ሰዎች ሁሉ ለዓለማት ጌታ (ፍርድ)፤ በሚቆሙበት ቀን (ተቀስቃሾች መኾናቸውን)፡፡
በእውነት የከሓዲዎቹ (የሰላቢዎቹ) መጽሐፍ በእርግጥ በሲጂን ውስጥ ነው፡፡
Verse 8
ሲጂንም ምን እንደ ኾነ ምን አሳወቀህ?
Verse 9
የታተመ መጽሐፍ ነው፡፡
Verse 10
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
Verse 11
ለእነዚያ በፍርዱ ቀን ለሚያስተባብሉት፡፡
በእርሱም ወሰን አላፊ ኀጢአተኛ ሁሉ እንጅ ሌላ አያስተባብልም፡፡
አንቀጾቻችን በእርሱ ላይ በተነበቡ ጊዜ «የመጀመሪያዎቹ ሰዎች ተረቶች ናቸው» ይላል፡፡
ይከልከል፤ ይልቁንም በልቦቻቸው ላይ ይሠሩት የነበሩት (ኀጢአት) ደገደገባቸው፡፡
ይከልከሉ፤ እነርሱ በዚያ ቀን ከጌታቸው (ማየት) ተጋራጆች ናቸው፡፡
Verse 16
ከዚያም እነርሱ በእርግጥ ገሀነምን ገቢዎች ናቸው፡፡
ከዚያም «ይህ ያ በእርሱ ታስተባብሉበት የነበራችሁት ነው» ይባላሉ፡፡
በእውነቱ የእውነተኞቹ ምእምናን መጽሐፍ በዒሊዮን ውስጥ ነው፡፡
Verse 19
ዒሊዮንም ምን እንደ ኾነ ምን አሳወቀህ?
Verse 20
የታተመ መጽሐፍ ነው፡፡
Verse 21
ባለሟልዎቹ ይጣዱታል፡፡
Verse 22
እውነተኞቹ ምእምናን በእርግጥ በድሎት (ገነት) ውስጥ ናቸው፡፡
Verse 23
በባለ አጎበር አልጋዎች ላይ ኾነው ይመለከታሉ፡፡
በፊቶቻቸው ላይ የድሎትን ውበት ታውቃለህ፡፡
ማተሚያው ምስክ ከኾነ፤ በዚህም ተሽቀዳዳሚዎች ይሽቀዳደሙ፡፡
Verse 27
መበረዣውም ከተስኒም ነው፡፡
Verse 28
ባለሟሎቹ ከእርሷ የሚጠጡላት ምንጭ ናት፡፡
Verse 30
በእነርሱም ላይ ባለፉ ጊዜ ይጠቃቀሱ ነበር፡፡
ወደ ቤተሰቦቻቸውም በተመለሱ ጊዜ (በመሳለቃቸው) ተደሳቾች ኾነው ይመለሱ ነበር፡፡
ባዩዋቸውም ጊዜ «እነዚህ በእርግጥ ተሳሳቾች ናቸው» ይሉ ነበር፡፡
Verse 33
በነርሱ ላይ ተጠባባቂዎች ተደርገው ያልተላኩ ሲኾኑ፡፡
ዛሬ (በትንሣኤ ቀን) እነዚያ ያመኑት በከሓዲዎቹ ይስቃሉ፡፡
Verse 35
በባለ አጎበር አልጋዎች ላይ ኾነው የሚመለከቱ ሲኾኑ (ይስቃሉ)፡፡
ከሓዲዎች ይሠሩት የነበሩትን (ዋጋ) ተመነዱን? (ይላሉ)፡፡
تقدم القراءة