የሱራ المطفّفين ትርጉም በالأمهرية ከالترجمة الأمهرية
Verse 1
ﯖﯗ
ﯘ
ለሰላቢዎች ወዮላቸው፡፡
Verse 2
ﯙﯚﯛﯜﯝﯞ
ﯟ
ለእነዚያ ከሰዎች ባስሰፈሩ ጊዜ የሚያስሞሉ፡፡
Verse 3
ﯠﯡﯢﯣﯤ
ﯥ
ለእነርሱም (ለሰዎቹ) በሰፈሩ ወይም በመዘኑላቸው ጊዜ የሚያጎድሉ (ለኾኑት)፡፡
Verse 4
ﯦﯧﯨﯩﯪ
ﯫ
እነዚያ እነርሱ ተቀስቃሾች መኾናቸውን አያውቁምን?
Verse 5
ﭑﭒ
ﭓ
በታላቁ ቀን፡፡
Verse 6
ﭔﭕﭖﭗﭘ
ﭙ
ሰዎች ሁሉ ለዓለማት ጌታ (ፍርድ)፤ በሚቆሙበት ቀን (ተቀስቃሾች መኾናቸውን)፡፡
Verse 7
ﭚﭛﭜﭝﭞﭟ
ﭠ
በእውነት የከሓዲዎቹ (የሰላቢዎቹ) መጽሐፍ በእርግጥ በሲጂን ውስጥ ነው፡፡
Verse 8
ﭡﭢﭣﭤ
ﭥ
ሲጂንም ምን እንደ ኾነ ምን አሳወቀህ?
Verse 9
ﭦﭧ
ﭨ
የታተመ መጽሐፍ ነው፡፡
Verse 10
ﭩﭪﭫ
ﭬ
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
Verse 11
ﭭﭮﭯﭰ
ﭱ
ለእነዚያ በፍርዱ ቀን ለሚያስተባብሉት፡፡
Verse 12
በእርሱም ወሰን አላፊ ኀጢአተኛ ሁሉ እንጅ ሌላ አያስተባብልም፡፡
Verse 13
አንቀጾቻችን በእርሱ ላይ በተነበቡ ጊዜ «የመጀመሪያዎቹ ሰዎች ተረቶች ናቸው» ይላል፡፡
Verse 14
ይከልከል፤ ይልቁንም በልቦቻቸው ላይ ይሠሩት የነበሩት (ኀጢአት) ደገደገባቸው፡፡
Verse 15
ﮍﮎﮏﮐﮑﮒ
ﮓ
ይከልከሉ፤ እነርሱ በዚያ ቀን ከጌታቸው (ማየት) ተጋራጆች ናቸው፡፡
Verse 16
ﮔﮕﮖﮗ
ﮘ
ከዚያም እነርሱ በእርግጥ ገሀነምን ገቢዎች ናቸው፡፡
Verse 17
ከዚያም «ይህ ያ በእርሱ ታስተባብሉበት የነበራችሁት ነው» ይባላሉ፡፡
Verse 18
ﮡﮢﮣﮤﮥﮦ
ﮧ
በእውነቱ የእውነተኞቹ ምእምናን መጽሐፍ በዒሊዮን ውስጥ ነው፡፡
Verse 19
ﮨﮩﮪﮫ
ﮬ
ዒሊዮንም ምን እንደ ኾነ ምን አሳወቀህ?
Verse 20
ﮭﮮ
ﮯ
የታተመ መጽሐፍ ነው፡፡
Verse 21
ﮰﮱ
ﯓ
ባለሟልዎቹ ይጣዱታል፡፡
Verse 22
ﯔﯕﯖﯗ
ﯘ
እውነተኞቹ ምእምናን በእርግጥ በድሎት (ገነት) ውስጥ ናቸው፡፡
Verse 23
ﯙﯚﯛ
ﯜ
በባለ አጎበር አልጋዎች ላይ ኾነው ይመለከታሉ፡፡
Verse 24
ﯝﯞﯟﯠﯡ
ﯢ
በፊቶቻቸው ላይ የድሎትን ውበት ታውቃለህ፡፡
Verse 25
ﯣﯤﯥﯦ
ﯧ
ተጣርቶ ከታተመ ጠጅ ይጠጣሉ፡፡
Verse 26
ማተሚያው ምስክ ከኾነ፤ በዚህም ተሽቀዳዳሚዎች ይሽቀዳደሙ፡፡
Verse 27
ﯰﯱﯲ
ﯳ
መበረዣውም ከተስኒም ነው፡፡
Verse 28
ﯴﯵﯶﯷ
ﯸ
ባለሟሎቹ ከእርሷ የሚጠጡላት ምንጭ ናት፡፡
Verse 29
እነዚያ ያምመጹት በእነዚያ ባመኑት በእርግጥ ይስቁ ነበሩ፡፡
Verse 30
ﰂﰃﰄﰅ
ﰆ
በእነርሱም ላይ ባለፉ ጊዜ ይጠቃቀሱ ነበር፡፡
Verse 31
ﰇﰈﰉﰊﰋﰌ
ﰍ
ወደ ቤተሰቦቻቸውም በተመለሱ ጊዜ (በመሳለቃቸው) ተደሳቾች ኾነው ይመለሱ ነበር፡፡
Verse 32
ﰎﰏﰐﰑﰒﰓ
ﰔ
ባዩዋቸውም ጊዜ «እነዚህ በእርግጥ ተሳሳቾች ናቸው» ይሉ ነበር፡፡
Verse 33
ﰕﰖﰗﰘ
ﰙ
በነርሱ ላይ ተጠባባቂዎች ተደርገው ያልተላኩ ሲኾኑ፡፡
Verse 34
ﭑﭒﭓﭔﭕﭖ
ﭗ
ዛሬ (በትንሣኤ ቀን) እነዚያ ያመኑት በከሓዲዎቹ ይስቃሉ፡፡
Verse 35
ﭘﭙﭚ
ﭛ
በባለ አጎበር አልጋዎች ላይ ኾነው የሚመለከቱ ሲኾኑ (ይስቃሉ)፡፡
Verse 36
ﭜﭝﭞﭟﭠﭡ
ﭢ
ከሓዲዎች ይሠሩት የነበሩትን (ዋጋ) ተመነዱን? (ይላሉ)፡፡
تقدم القراءة