سورة المطففين

Sadiq and Sani - Amharic translation

የሱራ المطفّفين ትርጉም በالأمهرية ከSadiq and Sani - Amharic translation

Sadiq and Sani - Amharic translation

Verse 1


ለሰላቢዎች ወዮላቸው፡፡

ለእነርሱም (ለሰዎቹ) በሰፈሩ ወይም በመዘኑላቸው ጊዜ የሚያጎድሉ (ለኾኑት)፡፡

እነዚያ እነርሱ ተቀስቃሾች መኾናቸውን አያውቁምን?

ሰዎች ሁሉ ለዓለማት ጌታ (ፍርድ)፤ በሚቆሙበት ቀን (ተቀስቃሾች መኾናቸውን)፡፡

በእውነት የከሓዲዎቹ (የሰላቢዎቹ) መጽሐፍ በእርግጥ በሲጂን ውስጥ ነው፡፡
Verse 8

ሲጂንም ምን እንደ ኾነ ምን አሳወቀህ?
Verse 9

የታተመ መጽሐፍ ነው፡፡
Verse 10

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
Verse 11

ለእነዚያ በፍርዱ ቀን ለሚያስተባብሉት፡፡

በእርሱም ወሰን አላፊ ኀጢአተኛ ሁሉ እንጅ ሌላ አያስተባብልም፡፡

አንቀጾቻችን በእርሱ ላይ በተነበቡ ጊዜ «የመጀመሪያዎቹ ሰዎች ተረቶች ናቸው» ይላል፡፡

ይከልከል፤ ይልቁንም በልቦቻቸው ላይ ይሠሩት የነበሩት (ኀጢአት) ደገደገባቸው፡፡

ይከልከሉ፤ እነርሱ በዚያ ቀን ከጌታቸው (ማየት) ተጋራጆች ናቸው፡፡
Verse 16

ከዚያም እነርሱ በእርግጥ ገሀነምን ገቢዎች ናቸው፡፡

ከዚያም «ይህ ያ በእርሱ ታስተባብሉበት የነበራችሁት ነው» ይባላሉ፡፡

በእውነቱ የእውነተኞቹ ምእምናን መጽሐፍ በዒሊዮን ውስጥ ነው፡፡
Verse 19

ዒሊዮንም ምን እንደ ኾነ ምን አሳወቀህ?
Verse 20

የታተመ መጽሐፍ ነው፡፡
Verse 21

ባለሟልዎቹ ይጣዱታል፡፡
Verse 22

እውነተኞቹ ምእምናን በእርግጥ በድሎት (ገነት) ውስጥ ናቸው፡፡
Verse 23

በባለ አጎበር አልጋዎች ላይ ኾነው ይመለከታሉ፡፡

በፊቶቻቸው ላይ የድሎትን ውበት ታውቃለህ፡፡

ማተሚያው ምስክ ከኾነ፤ በዚህም ተሽቀዳዳሚዎች ይሽቀዳደሙ፡፡
Verse 27

መበረዣውም ከተስኒም ነው፡፡
Verse 28

ባለሟሎቹ ከእርሷ የሚጠጡላት ምንጭ ናት፡፡
Verse 30

በእነርሱም ላይ ባለፉ ጊዜ ይጠቃቀሱ ነበር፡፡

ወደ ቤተሰቦቻቸውም በተመለሱ ጊዜ (በመሳለቃቸው) ተደሳቾች ኾነው ይመለሱ ነበር፡፡

ባዩዋቸውም ጊዜ «እነዚህ በእርግጥ ተሳሳቾች ናቸው» ይሉ ነበር፡፡
Verse 33

በነርሱ ላይ ተጠባባቂዎች ተደርገው ያልተላኩ ሲኾኑ፡፡

ዛሬ (በትንሣኤ ቀን) እነዚያ ያመኑት በከሓዲዎቹ ይስቃሉ፡፡
Verse 35

በባለ አጎበር አልጋዎች ላይ ኾነው የሚመለከቱ ሲኾኑ (ይስቃሉ)፡፡

ከሓዲዎች ይሠሩት የነበሩትን (ዋጋ) ተመነዱን? (ይላሉ)፡፡
تقدم القراءة