surah.translation .
من تأليف: محمد صادق ومحمد الثاني حبيب .

ልብህን ለአንተ አላሰፋንልህምን? (አስፍተንልሃል)፡፡
ሸክምህንም ካንተ አውርደንልሃል፡፡
ያንን ጀርባህን ያከበደውን (ሸክም)፡፡
መወሳትህንም ላንተ ከፍ አድርገንልሃል፡፡
ከችግርም ጋር ምቾት አልለ፡፡
ከችግር ጋር በእርግጥ ምቾት አልለ፡፡
በጨረስክም ጊዜ ልፋ፡፡ (ቀጥል)፡፡
ወደ ጌታህም ብቻ ከጅል፡፡