የሱራ الحجر ትርጉም በالأمهرية ከالترجمة الأمهرية
Verse 1
አ.ለ.ረ (አሊፍ ላም ራ) ይህች (አናቅጽ) ከመጽሐፉ አንቀጾችና ገላጭ ከኾነው ቁርኣን ናት፡፡
Verse 2
እነዚያ የካዱት (በትንሣኤ ቀን) ሙስሊሞች በኾኑ ኖሩ በብዛት ይመኛሉ፡፡
Verse 3
ተዋቸው ይብሉ፤ ይጠቀሙም፡፡ ተስፋም ያዘናጋቸው፡፡ በእርግጥም (መጥፎ ፍጻሜያቸውን) ያውቃሉ፡፡
Verse 4
ማንኛይቱንም ከተማ ለእርሷ የተወሰነ መጽሐፍ (ጊዜያት) ያላት ኾና እንጂ አላጠፋንም፡፡
Verse 5
ማንኛይቱም ሕዝብ ጊዜዋን ምንም አትቀድምም፡፡ (ከእርሱ) አይቆዩምም፡፡
Verse 6
«አንተ ያ በእርሱ ላይ ቁርኣን የተወረደለት ሆይ! አንተ በእርግጥ ዕብድ ነህ» አሉም፡፡
Verse 7
«ከእውነተኞቹ እንደ ኾንክ በመላእክት (መስካሪ) ለምን አትመጣንም» (አሉ)፡፡
Verse 8
መላእክትን በእውነት (በቅጣት) እንጂ አናወርድም፡፡ ያን ጊዜም የሚቆዩ አይደሉም፡፡
Verse 9
እኛ ቁርኣንን እኛው አወረድነው፡፡ እኛም ለእርሱ ጠባቂዎቹ ነን፡፡
Verse 10
ከአንተም በፊት በነበሩት በመጀመሪያዎቹ ሕዝቦች ውስጥ (መልክተኞችን) በእርግጥ ልከናል፡፡
Verse 11
ማንኛውም መልእክተኛ በእርሱ የሚያላግጡበት ኾነው እንጅ አይመጣቸውም ነበር፡፡
Verse 12
ﮰﮱﯓﯔﯕ
ﯖ
እንደዚሁ (ማስተባበልን) በአመጸኞቹ ልቦች ውስጥ እናገባዋለን፡፡
Verse 13
በእርሱ አያምኑበትም፡፡ የቀድሞዎቹም ድርጊት በእርግጥ አልፋለች፤ (እንደጠፉ ይጠፋሉ)፡፡
Verse 14
በእነርሱም ላይ ከሰማይ ደጃፍን በከፈትንላቸውና በእርሱ ሲወጡ በዋሉ ኖሮ፤
Verse 15
«የተዘጉት ዓይኖቻችን ናቸው፡፡ እንዲያውም እኛ የተደገመብን ሰዎች ነን» ባሉ ነበር፡፡
Verse 16
በሰማይም ላይ ቡርጆችን በእርግጥ አድርገናል፡፡ ለተመልካቾችም (በከዋክብት) አጊጠናታል፡፡
Verse 17
ﭙﭚﭛﭜﭝ
ﭞ
ከተባረረ ሰይጣንም ሁሉ ጠብቀናታል፡፡
Verse 18
ግን (ወሬ) መስማትን የሚሰርቅ ወዲየውኑ አብሪ ችቦ ይከተለዋል፡፡ (ያቃጥለዋል)፡፡
Verse 19
ምድርንም ዘረጋናት፡፡ በውስጧም ኮረብታዎችን ጣልናባት፡፡ በውስጧም (የተለካን) በቃይ ሁሉ አበቀልንባት፡፡
Verse 20
በእርሷም ውስጥ ለእናንተ መኖሪያዎችንና ለእርሱ መጋቢዎቹ ያልኾናችሁትንም (እንስሳትን) አደረግንላችሁ፡፡
Verse 21
መካዚኖቹም (መክፈቻቸው) እኛ ዘንድ ያልሆነ ምንም ነገር የለም፡፡ በተወሰነም ልክ እንጂ አናወርደውም፡፡
Verse 22
ነፋሶችንም (ደመናን) ተሸካሚዎች አድርገን ላክን፡፡ ከሰማይም (ከደመና) ዝናብን አወረድን፡፡ እርሱንም አጠጣናችሁ፡፡ እናንተም ለእርሱ አድላቢዎች አይደላችሁም፡፡
Verse 23
ﮕﮖﮗﮘﮙﮚ
ﮛ
እኛም ሕያው የምናደርግና የምንገድል እኛው ብቻ ነን፡፡ እኛም (ፍጡርን ሁሉ ) የምንወርስ (ቀሪ) ነን፡፡
Verse 24
ከእናንተም ተቀዳሚዎቹን በእርግጥ ዐውቀናል፡፡ ወደ ኋላም ቀሪዎቹን በእርግጥ ዐውቀናል፡፡
Verse 25
ጌታህም እርሱ ይሰበስባችኋል፡፡ እርሱ ጥበበኛ ዐዋቂ ነውና፡፡
Verse 26
ሰውንም ከሚቅጨለጨል ሸክላ ከሚገማ ጥቁር ጭቃ በእርግጥ ፈጠርነው፡፡
Verse 27
ጃንንም (ከሰው) በፊት ከእሳት ነበልባል ፈጠርነው፡፡
Verse 28
ጌታህም ለመላእክት ባለጊዜ (አስታውስ)፡፡ እኔ ሰውን ከሚቅጨለጨል ሸክላ ከሚገማ ጭቃ እፈጥራለሁ፡፡
Verse 29
(ፍጥረቱን) ባስተካከልኩትና በውስጡ ከመንፈሴ በነፋሁበትም ጊዜ ለእርሱ ሰጋጆች ኾናችሁ ውደቁ፡፡
Verse 30
ﯶﯷﯸﯹ
ﯺ
መላእክትም መላውም ተሰብስበው ሰገዱ፡፡
Verse 31
ኢብሊስ (ዲያብሎስ) ብቻ ሲቀር፡፡ ከሰጋጆቹ ጋር ከመኾን እንቢ አለ፡፡
Verse 32
(አላህም) «ኢብሊስ ሆይ! ከሰጋጆቹ ጋር የማትኾን ላንተ ምን ምክንያት አለህ» አለው፡፡
Verse 33
«ከሚቅጨለጨል ሸክላ ከግም ጭቃ ለፈጠርከው ሰው ልሰግድ አይገባኝም» አለ፡፡
Verse 34
ﭦﭧﭨﭩﭪ
ﭫ
(አላህ) አለው «ከርሷም ውጣ፡፡ አንተ የተባረርክ እርጉም ነህና፡፡»
Verse 35
ﭬﭭﭮﭯﭰﭱ
ﭲ
«ባንተ ላይም እስከ ፍርዱ ቀን ድረስ እርግማን አለብህ፡፡»
Verse 36
ﭳﭴﭵﭶﭷﭸ
ﭹ
«ጌታዬ ሆይ! እንግዲውያስ (ሰዎች) እስከሚቀሰቀሱበት ቀን ድረስ አቆየኝ» አለ፡፡
Verse 37
ﭺﭻﭼﭽ
ﭾ
(አላህም) አለ «አንተ ከሚቆዩት ነህ፡፡
Verse 38
ﭿﮀﮁﮂ
ﮃ
«እስከታወቀው ወቅት ቀን ድረስ፡፡»
Verse 39
(ኢብሊስ) አለ «ጌታዬ ሆይ! እኔን በማጥመምህ ይኹንብኝ ለነርሱ በምድር ላይ (ኀጢአትን) እሸልምላቸዋለሁ፡፡ ሁሉንም አጠማቸዋለሁም፡፡»
Verse 40
ﮏﮐﮑﮒ
ﮓ
«ከነርሱ ፍጹሞቹ ባሮችህ ብቻ ሲቀሩ፡፡»
Verse 41
ﮔﮕﮖﮗﮘ
ﮙ
(አላህም) አለ «ይህ በእኔ ላይ (መጠበቁ የተገባ) ቀጥተኛ መንገድ ነው፡፡»
Verse 42
«እነሆ ባሮቼ በእነሱ ላይ ላንተ ስልጣን የለህም፡፡ ከጠማሞቹ የተከተለህ ሰው ብቻ ሲቀር፡፡»
Verse 43
ﮦﮧﮨﮩ
ﮪ
«ገሀነምም (ለርሱና ለተከተሉት) ለመላውም በእርግጥ ቀጠሯቸው ናት፡፡
Verse 44
«ለእርሷ ሰባት ደጃፎች አሏት፡፡ ለየደጀፉም ሁሉ ከእነሱ የተከፈለ ፋንታ አለ፡፡
Verse 45
ﯕﯖﯗﯘﯙ
ﯚ
«እነዚያ (ከኀጢአት) የተጠነቀቁት በአትክልቶችና በምንጮች ውስጥ ናቸው፡፡
Verse 46
ﯛﯜﯝ
ﯞ
«ጸጥተኞች ኾናችሁ በሰላም ግቧት (ይባላሉ)፡፡
Verse 47
«ባልጋዎችም ላይ ፊት ለፊት የሚቅጣጩ ወንድማማቾች ኾነው በደረቶቻቸው ውስጥ ከቂም ያለውን ሁሉ እናስወግዳለን፡፡
Verse 48
«በእርሷም ውስጥ ድካም አይነካቸውም፡፡ እነሱም ከእርሷ የሚወጡ አይደሉም፡፡»
Verse 49
ባሮቼን እኔ መሓሪው አዛኙ እኔው ብቻ መኾኔን ንገራቸው፡፡
Verse 50
ﯻﯼﯽﯾﯿ
ﰀ
ቅጣቴም እርሱ አሳማሚ ቅጣት መኾኑን (ንገራቸው)፡፡
Verse 51
ﰁﰂﰃﰄ
ﰅ
ከኢብራሂም እንግዶችም (ወሬ) ንገራቸው፡፡
Verse 52
በእርሱ ላይ በገቡና ሰላም ባሉት ጊዜ የኾነውን (አስታውስ)፡፡ (እርሱም) «እኛ ከእናንተ ፈሪዎች ነን» አላቸው፡፡
Verse 53
«አትፍራ፤ እኛ ዐዋቂ በኾነ ወንድ ልጅ እናበስርሃለን» አሉት፡፡
Verse 54
«እርጅና የደረሰብኝ ከመኾኔ ጋር አበሰራችሁኝን በምን ታበስሩኛላችሁ» አለ፡፡
Verse 55
«በእውነት አበሰርንህ፡፡ ከተሰፋ ቆራጮችም አትኹን» አሉ፡፡
Verse 56
«ከጠማማዎችም በስተቀር ከጌታው እዝነት ተስፋን የሚቆርጥ ማነው» አለ፡፡
Verse 57
ﭽﭾﭿﮀﮁ
ﮂ
«እናንተ መልክተኞች ሆይ! ኧረ ለመኾኑ ነገራችሁ ምንድን ነው» አለ፡፡
Verse 58
ﮃﮄﮅﮆﮇﮈ
ﮉ
«እኛ አመጸኞች ወደ ኾኑ ሕዝቦች ተልከናል» አሉት፡፡
Verse 59
ﮊﮋﮌﮍﮎﮏ
ﮐ
«የሉጥ ቤተሰቦች ብቻ ሲቀሩ፡፡ (እነርሱን) እኛ ሁላቸውንም በእርግጥ የምናድናቸው ነን፡፡
Verse 60
ﮑﮒﮓﮔﮕﮖ
ﮗ
«ሚስቱ ብቻ ስትቀር፡፡ እርሷን (በቅጣቱ ውስጥ) ከሚቀሩት መኾኗን ወሰነናል» (አሉ)፡፡
Verse 61
ﮘﮙﮚﮛﮜ
ﮝ
መልክተኞቹም የሉጥን ቤተሰቦች በመጡባቸው ጊዜ፤
Verse 62
ﮞﮟﮠﮡ
ﮢ
(ሉጥ) «እናንተ የተሳታችሁ ሕዝቦች ናችሁ» አላቸው፡፡
Verse 63
«አይደለም እኛ ሕዝቦችህ በርሱ ይጠራጠሩበት በነበሩት ቅጣት መጣንህ» አሉት፡፡
Verse 64
ﮫﮬﮭﮮ
ﮯ
«እውነትንም ይዘን መጣንህ፡፡ እኛም በእርግጥ እውነተኞች ነን፡፡
Verse 65
ከቤተሰብህም ጋር በሌሊቱ ከፊል ኺድ፡፡ ከኋላቸውም ተከተል፡፡ ከእናንተም አንድም ሰው ወደ ኋላው አይገላመጥ፡፡ ወደ ታዘዛችሁበትም ስፍራ እለፉ» (አሉት)፡፡
Verse 66
ወደርሱም ያንን ትእዛዝ አወረድን፡፡ (እርሱም) የእነዚህ (ሕዝቦች) መጨረሻ ያነጉ ሲኾኑ (ሥራቸው) መቆረጥ ነው፡፡
Verse 67
ﯪﯫﯬﯭ
ﯮ
የከተማይቱም ሰዎች የሚበሳሰሩ ኾነው መጡ፡፡
Verse 68
ﯯﯰﯱﯲﯳﯴ
ﯵ
(ሉጥም) አለ «እነዚህ እንግዶቼ ናቸውና አታጋልጡኝ፡፡
Verse 69
ﯶﯷﯸﯹ
ﯺ
«አላህንም ፍሩ፤ አታሳፍሩኝም፡፡»
Verse 70
ﯻﯼﯽﯾﯿ
ﰀ
«ከዓለማት (ማንንም እንዳታስተናግድ) አልከለከልንህምን» አሉት፡፡
Verse 71
ﭑﭒﭓﭔﭕﭖ
ﭗ
(ሉጥም) «እነኝህ ሴቶች ልጆቼ ናቸው፡፡ ሠሪዎች ብትኾኑ (አግቧቸው)» አለ፡፡
Verse 72
ﭘﭙﭚﭛﭜ
ﭝ
በዕድሜህ እንምላለን እነሱ በእርግጥ በስከራቸው ውስጥ ይዋልላሉ፡፡
Verse 73
ﭞﭟﭠ
ﭡ
ጩኸቲቱም ፀሐይ የወጣችባቸው ሲኾኑ ያዘቻቸው፡፡
Verse 74
ላይዋንም ከታችዋ አደረግን፡፡ በእነሱም ላይ የሸክላ ደንጊያዎችን አዘነብንባቸው፡፡
Verse 75
ﭫﭬﭭﭮﭯ
ﭰ
በዚህ ውስጥ ለተመልካቾች በእርግጥ መገምገሚያዎች አሉበት፡፡
Verse 76
ﭱﭲﭳ
ﭴ
እሷም (ከተማይቱ) በቀጥታ መንገድ ላይ ናት፡፡
Verse 77
ﭵﭶﭷﭸﭹ
ﭺ
በዚህ ውስጥ በእርግጥ ለምእምናን መገሰጫ አለ፡፡
Verse 78
ﭻﭼﭽﭾﭿ
ﮀ
እነሆ የአይከት ሰዎችም በእርግጥ በዳዮች ነበሩ፤
Verse 79
ﮁﮂﮃﮄﮅ
ﮆ
ከነሱም ተበቀልን ሁለቱም (የሉጥና የአይከት ሕዝቦች ከተሞች) በእርግጥ በግልጽ መንገድ ላይ ናቸው፡፡
Verse 80
ﮇﮈﮉﮊﮋ
ﮌ
የሒጅርም ሰዎች መልክተኞቹን በእርግጥ አስተባበሉ፡፡
Verse 81
ﮍﮎﮏﮐﮑ
ﮒ
ተዓምራታችንንም ሰጠናቸው፡፡ ከእርሷም ዘንጊዎች ነበሩ፡፡
Verse 82
ﮓﮔﮕﮖﮗﮘ
ﮙ
ከኮረብታዎችም ቤቶችን ጸጥተኞች ኾነው ይጠርቡ ነበር፡፡
Verse 83
ﮚﮛﮜ
ﮝ
ያነጉም ሲኾኑ ጩኸት ያዘቻቸው፤ (ወደሙ)፡፡
Verse 84
ﮞﮟﮠﮡﮢﮣ
ﮤ
ይሠሩትም የነበሩት ሕንጻ ምንም አልጠቀማቸውም፡፡
Verse 85
ሰማያትንና ምድርንም በመካከላቸው ያለውንም ሁሉ በእውነት እንጂ (በላግጣ) አልፈጠርንም፡፡ ሰዓቲቱም በእርግጥ መጪ ናት፡፡ መልካምንም ይቅርታ አድርግላቸው፡፡
Verse 86
ﯗﯘﯙﯚﯛ
ﯜ
ጌታህ እርሱ (ያልነበረን) ፈጣሪው ዐዋቂው ነው፡፡
Verse 87
ከሚደጋገሙ የኾኑን ሰባትንና ታላቁንም ቁርኣን (በሙሉ) በእርግጥ ሰጠንህ፡፡
Verse 88
ከእነርሱ (ከከሓዲዎች) ብዙዎችን ወገኖች በእርሱ ወደ አጣቀምንበት ጸጋ ዓይኖችህን አትዘርጋ፡፡ በእነሱም ላይ (ባያምኑ) አትዘን፡፡ ክንፍህንም ለምእምናን አለዝብ፡፡
Verse 89
ﯵﯶﯷﯸﯹ
ﯺ
በልም «እኔ ግልጽ አስፈራሪው እኔ ነኝ፡፡»
Verse 90
ﯻﯼﯽﯾ
ﯿ
(ሰዎችን ለማገድ የመካን በሮች) በተከፋፈሉት ላይ እንደ አወረድነው (በኾነ ቅጣት አሰፈራሪያችሁ ነኝ በል)፡፡
Verse 91
ﭑﭒﭓﭔ
ﭕ
(እነርሱም) እነዚያ ቁርኣንንን ክፍልፍሎች ያደረጉ ናቸው፡፡
Verse 92
ﭖﭗﭘ
ﭙ
በጌታህም እንምላለን፡፡ ሁላቸውንም እንጠይቃቸዋለን፤
Verse 93
ﭚﭛﭜ
ﭝ
ይሠሩት ከነበሩት ነገር ሁሉ፡፡
Verse 94
ﭞﭟﭠﭡﭢﭣ
ﭤ
የታዘዝክበትንም ነገር በይፋ ግለጽ፡፡ አጋሪዎችንም ተዋቸው፡፡
Verse 95
ﭥﭦﭧ
ﭨ
ተሳላቂዎችን ሁሉ እኛ በቅተንሃል፡፡
Verse 96
(እነሱም) እነዚያ ከአላህ ጋር ሌላ አምላክን ያደረጉ ናቸው፡፡ በእርግጥም (ፍጻሜያቸውን) ወደፊት ያውቃሉ፡፡
Verse 97
አንተም በሚሉት ነገር ልብህ የሚጠብ መኾኑን በእርግጥ እናውቃለን፡፡
Verse 98
ﭻﭼﭽﭾﭿﮀ
ﮁ
ጌታህንም ከማመስገን ጋር አጥራው ከሰጋጆቹም ኹን፡፡
Verse 99
ﮂﮃﮄﮅﮆ
ﮇ
እውነቱም (ሞት) እስኪመጣህ ድረስ ጌታህን ተገዛ፡፡
تقدم القراءة