የሱራ الإنشقاق ትርጉም በالأمهرية ከالترجمة الأمهرية
Verse 1
ﭣﭤﭥ
ﭦ
ሰማይ በተቀደደች ጊዜ፤
Verse 2
ﭧﭨﭩ
ﭪ
ለጌታዋም (ትዕዛዝ) በሰማች ጊዜ፤ (ልትሰማ) ተገባትም፤
Verse 3
ﭫﭬﭭ
ﭮ
ምድርም በተለጠጠች ጊዜ፤
Verse 4
ﭯﭰﭱﭲ
ﭳ
በውስጧ ያለውንም ሁሉ በጣለችና ባዶ በኾነች ጊዜ፤
Verse 5
ﭴﭵﭶ
ﭷ
ለጌታዋም በሰማች ጊዜ፤ (መስማት) ተገባትም፤ (ሰው ሁሉ ሥራውን ይገናኛል)፡፡
Verse 6
አንተ ሰው ሆይ! አንተ ጌታህን (በሞት) እስከምትገናኝ ድረስ ልፋትን ለፊ ነህ፤ ተገናኚውም ነህ፡፡
Verse 7
ﮁﮂﮃﮄﮅ
ﮆ
መጽሐፉን በቀኙ የተሰጠ ሰውማ፤
Verse 8
ﮇﮈﮉﮊ
ﮋ
በእርግጥ ቀላልን ምርመራ ይመረመራል፡፡
Verse 9
ﮌﮍﮎﮏ
ﮐ
ወደ ቤተሰቦቹም ተደሳች ኾኖ ይመለሳል፡፡
Verse 10
ﮑﮒﮓﮔﮕﮖ
ﮗ
መጽሐፉን በጀርባው ኋላ የተሰጠ ሰውማ፤
Verse 11
ﮘﮙﮚ
ﮛ
(ዋ! ጥፋቴ በማለት) ጥፋትን በእርግጥ ይጠራል፡፡
Verse 12
ﮜﮝ
ﮞ
የተጋጋመች እሳትንም ይገባል፡፡
Verse 13
ﮟﮠﮡﮢﮣ
ﮤ
እርሱ በቤተሰቡ ውስጥ ተደሳች ነበርና፡፡
Verse 14
ﮥﮦﮧﮨﮩ
ﮪ
እርሱ (ወደ አላህ) የማይመለስ መኾኑን አስቧልና፡፡
Verse 15
አይደለም (ይመለሳል)፡፡ ጌታው በእርሱ (መመለስ) ዐዋቂ ነበር፤ (ነውም)፡፡
Verse 16
ﯔﯕﯖ
ﯗ
አትካዱ፤ በወጋገኑ እምላለሁ፡፡
Verse 17
ﯘﯙﯚ
ﯛ
በሌሊቱም በሰበሰውም ሁሉ፤
Verse 18
ﯜﯝﯞ
ﯟ
በጨረቃውም በሞላ ጊዜ (እምላለሁ)፡፡
Verse 19
ﯠﯡﯢﯣ
ﯤ
ከኹነታ በኋላ ወደ ሌላ ኹነታ ትለዋወጣላችሁ፡፡
Verse 20
ﯥﯦﯧﯨ
ﯩ
የማያምኑት ለእነርሱ ምን አላቸው?
Verse 21
በእነርሱም ላይ ቁርኣን በተነበበ ጊዜ የማይሰግዱት፤ (ምንአላቸው?)
Verse 22
ﯲﯳﯴﯵ
ﯶ
በእርግጡ እነዚያ የካዱት (በትንሣኤ) ያስተባብላሉ፡፡
Verse 23
ﯷﯸﯹﯺ
ﯻ
አላህም (በልቦቻቸው) የሚቆጥሩትን ዐዋቂ ነው፡፡
Verse 24
ﯼﯽﯾ
ﯿ
በአሳማሚ ቅጣትም አብስራቸው፡፡
Verse 25
ግን እነዚያ ያመኑና መልካሞችን የሠሩ ለእነርሱ የማይቆረጥ ምንዳ አልላቸው፡፡
تقدم القراءة