የሱራ المعارج ትርጉም በالأمهرية ከالترجمة الأمهرية
Verse 1
ﮮﮯﮰﮱ
ﯓ
ወዳቂ ከኾነው ቅጣት ጠያቂ ጠየቀ፡፡
Verse 2
ﯔﯕﯖﯗ
ﯘ
በከሓዲዎች ላይ (ወዳቂ ከኾነው) ለእርሱ መላሽ የለውም፡፡
Verse 3
ﯙﯚﯛﯜ
ﯝ
የ(ሰማያት) መሰላሎች ባለቤት ከኾነው አላህ (መላሽ የለውም)፡፡
Verse 4
መላእክቱና መንፈሱም ልኩ አምሳ ሺሕ ዓመት በኾነ ቀን ውስጥ ወደእርሱ ያርጋሉ፤ (ይወጣሉ)፡፡
Verse 5
ﯪﯫﯬ
ﯭ
መልካምንም ትዕግስት ታገሥ፡፡
Verse 6
ﯮﯯﯰ
ﯱ
እነርሱ (ያንን ቀን) ሩቅ አድርገው ያዩታል፡፡
Verse 7
ﯲﯳ
ﯴ
እኛም ቅርብ ኾኖ እናየዋለን፡፡
Verse 8
ﯵﯶﯷﯸ
ﯹ
ሰማይ እንደ ዘይት አተላ በምትኾንበት ቀን፡፡
Verse 9
ﯺﯻﯼ
ﯽ
ጋራዎችም በተለያዩ ቀለማት እንደ ተነከረ ሱፍ (ነፋስ እንደሚያበረው) በሚኾኑበት ቀን፡፡
Verse 10
ﯾﯿﰀﰁ
ﰂ
ዘመድም ዘመድን በማይጠይቅበት ቀን፤ (መላሽ የለውም)፡፡
Verse 11
(ዘመዶቻቸውን) ያዩዋቸዋል፡፡ አመጸኛው ከዚያ ቀን ስቃይ (ነፍሱን) በልጆቹ ሊበዥ ይመኛል፡፡
Verse 12
ﭜﭝ
ﭞ
በሚስቱም በወንድሙም፡፡
Verse 13
ﭟﭠﭡ
ﭢ
በዚያችም በምታስጠጋው ጎሳው፡፡
Verse 14
ﭣﭤﭥﭦﭧﭨ
ﭩ
በምድርም ላይ ባለው ሁሉ (ሊበዥ) ከዚያም ሊያድነው (ይመኛል)፡፡
Verse 15
ﭪﭫﭬﭭ
ﭮ
ይተው! እርሷ (እሳቲቱ) ለዟ ናት፡፡
Verse 16
ﭯﭰ
ﭱ
የራስን ቅል ቆዳ የምትሞሽልቅ ስትኾን፡፡
Verse 17
ﭲﭳﭴﭵ
ﭶ
(ከእምነት) የዞረንና የሸሸን ሰው (ወደእርሷ) ትጠራለች፡፡
Verse 18
ﭷﭸ
ﭹ
ገንዘብን የሰበሰበንና (ዘካውን ሳይሰጥ) የቆጠረንም፤ (ትጠራለች)፡፡
Verse 19
ﭺﭻﭼﭽﭾ
ﭿ
ሰው ቅጠ ቢስ ኾኖ ተፈጠረ፡፡
Verse 20
ﮀﮁﮂﮃ
ﮄ
ክፉ ነገር ባገኘው ጊዜ ብስጪተኛ፡፡
Verse 21
ﮅﮆﮇﮈ
ﮉ
መልካምም ነገር (ድሎት) ባገኘ ጊዜ ከልካይ (ኾኖ ተፈጠረ)፡፡
Verse 22
ﮊﮋ
ﮌ
ሰጋጆቹ ብቻ ሲቀሩ፡፡
Verse 23
ﮍﮎﮏﮐﮑ
ﮒ
እነዚያ እነርሱ በስግደታቸው ላይ ዘውታሪዎች የኾኑት፡፡
Verse 24
ﮓﮔﮕﮖﮗ
ﮘ
እነዚያም በገንዘቦቻቸው ላይ የታወቀ መብት ያለባቸው የኾኑት፡፡
Verse 25
ﮙﮚ
ﮛ
ለለማኝ ከልመና ለሚከለከልም (መብት ያለባቸው የኾኑት)፡፡
Verse 26
ﮜﮝﮞﮟ
ﮠ
እነዚያም በፍርዱ ቀን እውነት የሚሉት (የሚያረጋግጡት)፡፡
Verse 27
ﮡﮢﮣﮤﮥﮦ
ﮧ
እነዚያም እነርሱ ከጌታቸው ቅጣት ፈሪዎች የኾኑት፡፡
Verse 28
ﮨﮩﮪﮫﮬ
ﮭ
የጌታቸው ቅጣት (መምጣቱ) የማያስተማምን ነውና፡፡
Verse 29
ﮮﮯﮰﮱ
ﯓ
እነዚያም እነርሱ ብልቶቻቸውን ጠባቂዎች የኾኑት፡፡
Verse 30
በሚስቶቻቸው ወይም እጆቻቸው በያዙዋቸው (ባሪያዎች) ላይ ሲቀር፡፡ እነርሱ (በእነዚህ) የማይወቀሱ ናቸውና፡፡
Verse 31
ከዚያም ወዲያ የፈለገ ሰው እነዚያ እነሱ ድንበር አላፊዎች ናቸው፡፡
Verse 32
ﯧﯨﯩﯪﯫ
ﯬ
እነዚያም እነርሱ አደራዎቻቸውንና ቃል ኪዳናቸውን ጠባቂዎች የኾኑት፡፡
Verse 33
ﯭﯮﯯﯰ
ﯱ
እነዚያም እነርሱ በምስክርነታቸው ትክክለኞች የኾኑት፡፡
Verse 34
ﯲﯳﯴﯵﯶ
ﯷ
እነዚያም እነርሱ በሶላቶቻቸው ላይ የሚጠባበቁት፡፡
Verse 35
ﯸﯹﯺﯻ
ﯼ
እነዚህ (ከዚህ በላይ የተወሱት ሁሉ) በገነቶች ውስጥ የሚከበሩ ናቸው፡፡
Verse 36
ﯽﯾﯿﰀﰁ
ﰂ
ለእነዚያም ለካዱት ወደ አንተ በኩል አንገቶቻቸውን መዝዘው የሚያተኩሩት ምን አላቸው?
Verse 37
ﰃﰄﰅﰆﰇ
ﰈ
ከቀኝና ከግራ ክፍልፍል ጭፍሮች ሲኾኑ፡፡
Verse 38
ከእነርሱ እያንዳንዱ ሰው የጸጋይቱን ገነት መግባትን ይከጅላልን?
Verse 39
ﰒﰓﰔﰕﰖﰗ
ﰘ
ይከልከል፤ እኛ ከሚያውቁት ነገር (ከፍቶት ጠብታ) ፈጠርናቸው፡፡
Verse 40
በምሥራቆችና በምዕራቦችም ጌታ እምላለሁ፡፡ እኛ በእርግጥ ቻዮች ነን፡፡
Verse 41
ከእነርሱ የተሻለን በመለወጥ ላይ፡፡ እኛም ተሸናፊዎች አይደለንም፡፡
Verse 42
ያንንም የሚስፈራሩበትን ቀናቸውን እስከሚገናኙ ድረስ ተዋቸው፡፡ ይዋኙ ይጫወቱም፡፡
Verse 43
ወደ ጣዖቶች እንደሚሽቀዳደሙ ኾነው ከመቃብሮቻቸው ፈጥነው የሚወጡበትን ቀን (እስከሚገናኙ ድረስ ተዋቸው)፡፡
Verse 44
ዓይኖቻቸው ያፈሩ ኾነው ውርደት ትሸፍናቸዋለች፡፡ ይህ ቀን ያ ይስፈራሩበት የነበሩት ነው፡፡
تقدم القراءة