سورة المعارج

Sadiq and Sani - Amharic translation

የሱራ المعارج ትርጉም በالأمهرية ከSadiq and Sani - Amharic translation

Sadiq and Sani - Amharic translation

Verse 2

በከሓዲዎች ላይ (ወዳቂ ከኾነው) ለእርሱ መላሽ የለውም፡፡
Verse 3

የ(ሰማያት) መሰላሎች ባለቤት ከኾነው አላህ (መላሽ የለውም)፡፡

መላእክቱና መንፈሱም ልኩ አምሳ ሺሕ ዓመት በኾነ ቀን ውስጥ ወደእርሱ ያርጋሉ፤ (ይወጣሉ)፡፡
Verse 5

መልካምንም ትዕግስት ታገሥ፡፡
Verse 6

እነርሱ (ያንን ቀን) ሩቅ አድርገው ያዩታል፡፡
Verse 7

እኛም ቅርብ ኾኖ እናየዋለን፡፡
Verse 8

ሰማይ እንደ ዘይት አተላ በምትኾንበት ቀን፡፡
Verse 9

ጋራዎችም በተለያዩ ቀለማት እንደ ተነከረ ሱፍ (ነፋስ እንደሚያበረው) በሚኾኑበት ቀን፡፡
Verse 10

ዘመድም ዘመድን በማይጠይቅበት ቀን፤ (መላሽ የለውም)፡፡

(ዘመዶቻቸውን) ያዩዋቸዋል፡፡ አመጸኛው ከዚያ ቀን ስቃይ (ነፍሱን) በልጆቹ ሊበዥ ይመኛል፡፡
Verse 12

በሚስቱም በወንድሙም፡፡
Verse 13

በዚያችም በምታስጠጋው ጎሳው፡፡

በምድርም ላይ ባለው ሁሉ (ሊበዥ) ከዚያም ሊያድነው (ይመኛል)፡፡
Verse 16

የራስን ቅል ቆዳ የምትሞሽልቅ ስትኾን፡፡
Verse 17

(ከእምነት) የዞረንና የሸሸን ሰው (ወደእርሷ) ትጠራለች፡፡
Verse 18

ገንዘብን የሰበሰበንና (ዘካውን ሳይሰጥ) የቆጠረንም፤ (ትጠራለች)፡፡
Verse 20

ክፉ ነገር ባገኘው ጊዜ ብስጪተኛ፡፡
Verse 21

መልካምም ነገር (ድሎት) ባገኘ ጊዜ ከልካይ (ኾኖ ተፈጠረ)፡፡
Verse 22

ሰጋጆቹ ብቻ ሲቀሩ፡፡

እነዚያ እነርሱ በስግደታቸው ላይ ዘውታሪዎች የኾኑት፡፡

እነዚያም በገንዘቦቻቸው ላይ የታወቀ መብት ያለባቸው የኾኑት፡፡
Verse 25

ለለማኝ ከልመና ለሚከለከልም (መብት ያለባቸው የኾኑት)፡፡
Verse 26

እነዚያም በፍርዱ ቀን እውነት የሚሉት (የሚያረጋግጡት)፡፡

እነዚያም እነርሱ ከጌታቸው ቅጣት ፈሪዎች የኾኑት፡፡

የጌታቸው ቅጣት (መምጣቱ) የማያስተማምን ነውና፡፡
Verse 29

እነዚያም እነርሱ ብልቶቻቸውን ጠባቂዎች የኾኑት፡፡

በሚስቶቻቸው ወይም እጆቻቸው በያዙዋቸው (ባሪያዎች) ላይ ሲቀር፡፡ እነርሱ (በእነዚህ) የማይወቀሱ ናቸውና፡፡

ከዚያም ወዲያ የፈለገ ሰው እነዚያ እነሱ ድንበር አላፊዎች ናቸው፡፡

እነዚያም እነርሱ አደራዎቻቸውንና ቃል ኪዳናቸውን ጠባቂዎች የኾኑት፡፡
Verse 33

እነዚያም እነርሱ በምስክርነታቸው ትክክለኞች የኾኑት፡፡

እነዚያም እነርሱ በሶላቶቻቸው ላይ የሚጠባበቁት፡፡
Verse 35

እነዚህ (ከዚህ በላይ የተወሱት ሁሉ) በገነቶች ውስጥ የሚከበሩ ናቸው፡፡

ለእነዚያም ለካዱት ወደ አንተ በኩል አንገቶቻቸውን መዝዘው የሚያተኩሩት ምን አላቸው?

ከእነርሱ እያንዳንዱ ሰው የጸጋይቱን ገነት መግባትን ይከጅላልን?

ይከልከል፤ እኛ ከሚያውቁት ነገር (ከፍቶት ጠብታ) ፈጠርናቸው፡፡

በምሥራቆችና በምዕራቦችም ጌታ እምላለሁ፡፡ እኛ በእርግጥ ቻዮች ነን፡፡

ከእነርሱ የተሻለን በመለወጥ ላይ፡፡ እኛም ተሸናፊዎች አይደለንም፡፡

ያንንም የሚስፈራሩበትን ቀናቸውን እስከሚገናኙ ድረስ ተዋቸው፡፡ ይዋኙ ይጫወቱም፡፡

ወደ ጣዖቶች እንደሚሽቀዳደሙ ኾነው ከመቃብሮቻቸው ፈጥነው የሚወጡበትን ቀን (እስከሚገናኙ ድረስ ተዋቸው)፡፡

ዓይኖቻቸው ያፈሩ ኾነው ውርደት ትሸፍናቸዋለች፡፡ ይህ ቀን ያ ይስፈራሩበት የነበሩት ነው፡፡
تقدم القراءة