سورة النبأ

Sadiq and Sani - Amharic translation

የሱራ النبأ ትርጉም በالأمهرية ከSadiq and Sani - Amharic translation

Sadiq and Sani - Amharic translation

Verse 1


ከምን ነገር ይጠያየቃሉ?
Verse 2

ከታላቁ ዜና (ከቁርኣን ይጠያየቃሉ)፡፡
Verse 3

ከዚያ እነርሱ በእርሱ የተለያዩበት ከኾነው፡፡
Verse 4

ይከልከሉ፤ ወደፊት (የሚደርስበቸውን) በእርግጥ ያውቃሉ፡፡
Verse 5

ከዚያም ይከልከሉ፤ ወደፊት ያውቃሉ፡፡
Verse 7

ጋራዎችንም ችካሎች አላደረግንምን?
Verse 8

ብዙ ዓይነቶችም አድርገን ፈጠርናችሁ፡፡
Verse 9

እንቅልፋችሁንም ዕረፍት አደረግን፡፡
Verse 10

ሌሊቱንም ልባስ አደረግን፡፡
Verse 11

ቀኑንም (ለኑሮ) መስሪያ አደረግን፡፡
Verse 12

ከበላያችሁም ሰባትን ብርቱዎች (ሰማያት) ገነባን፡፡
Verse 13

አንጸባራቂ ብርሃንንም አደረግን፡፡

ከአረገዙት ደመናዎችም ተንቧቢ ውሃን አወረድን፡፡
Verse 15

በእርሱ እኽልንና ቅጠላ ቅጠልን እናወጣ ዘንድ (አወረድን)፡፡
Verse 16

የተቆላለፉ አትክልቶችንም፡፡

በቀንዱ በሚነፋና የተለያዩ ጭፍሮች ኾናችሁ በምትመጡ ቀን ነው፡፡
Verse 19

ሰማይም በምትከፈትና (ባለ) ደጃፎችም በምትኾንበት፡፡
Verse 20

ጋራዎችም በሚነዱበት (እንደ) ሲሪብዱም በሚኾኑበት (ቀን) ነው፡፡
Verse 22

ለሕግ ተላላፊዎች መመለሻ ስትኾን፡፡
Verse 23

በውስጧ ብዙን ዘመናት ነዋሪዎች ሲኾኑ፤
Verse 25

ግን ሙቅ ውሃንና እዥን (ይቀምሳሉ)፡፡
Verse 26

ተስማሚን ምንዳ ይምመነዳሉ፡፡
Verse 28

በአንቀጾቻችንም ማስተባበልን አስተባበሉና፡፡
Verse 29

ነገሩንም ሁሉ የተጻፈ ሲኾን አጠቃለልነው፡፡

ቅመሱም ቅጣትንም እንጅ (ሌላን) አንጨምራችሁም (ይባላሉ)፡፡
Verse 31

ለጥንቁቆቹ መዳኛ ስፍራ አልላቸው፡፡
Verse 32

አትክልቶችና ወይኖችም፡፡
Verse 33

እኩያዎች የኾኑ ጡተ ጉቻማዎችም፡፡
Verse 34

የተሞሉ ብርጭቆዎችም፡፡

ከጌታህ የኾነን ምንዳ በቂ ስጦታን (ተሰጡ)፡፡

የሰማያትና የምድር በመካከላቸውም ያለው ሁሉ ጌታ በጣም አዛኝ ከኾነው (ተመነዱ)፡፡ ከእርሱ ጋር መነጋገርን አይችሉም፡፡

መንፈሱ (ጂብሪል) መላእክቶቹም የተሰለፉ ኾነው በሚቆሙ ቀን አል-ረሕማን ለእርሱ የፈቀደለትና ትክክለኛን ቃል ያለ ሰው ቢኾን እንጅ (መነጋገርን አይችሉም)፡፡

እኛ ሰው ሁሉ እጆቹ ያስቀደሙትን በሚያይበትና ከሓዲውም ዋ ምኞቴ! ምንነው ዐፈር በኾንኩ በሚልበት ቀን ቅርብ የኾነን ቅጣት አስጠነቀቅናችሁ፡፡
تقدم القراءة