የሱራ الدّخان ትርጉም በالأمهرية ከSadiq and Sani - Amharic translation
Verse 1
ﭑ
ﭒ
ሐ.መ (ሓ ሚም)፡፡
Verse 2
ﭓﭔ
ﭕ
አብራሪ በኾነው መጽሐፍ እንምላለን፡፡
Verse 3
እኛ (ቁርኣኑን) በተባረከች ሌሊት ውስጥ አወረድነው፡፡ እኛ አስፈራሪዎች ነበርንና፡፡
Verse 4
ﭠﭡﭢﭣﭤ
ﭥ
በውስጧ የተወሰነው ነገር ሁሉ ይልለያል፡፡
Verse 5
ከእኛ ዘንድ የኾነ ትእዛዝ ሲኾን (አወረድነው)፡፡ እኛ (መልክተኞችን) ላኪዎች ነበርን፡፡
Verse 6
ከጌታህ በኾነው ችሮታ (ተላኩ)፡፡ እነሆ እርሱ ሰሚው ዐዋቂው ነውና፡፡
Verse 7
የሰማያትና የምድር በመካከላቸውም ያለው ነገር ሁሉ ጌታ ከኾነው (ተላኩ)፡፡ የምታረጋግጡ እንደኾናችሁ (ነገሩ እንዳልነው መኾኑን እወቁ)፡፡
Verse 8
ከእርሱ ሌላ አምላክ የለም፡፡ ሕያው ያደርጋል፡፡ ይገድላልም፡፡ ጌታችሁ የመጀመሪያዎቹ አባቶቻችሁም ጌታ ነው፡፡
Verse 9
ﮍﮎﮏﮐﮑ
ﮒ
በእውነቱ እነርሱ የሚጫወቱ ሲኾኑ በመጠራጠር ውስጥ ናቸው፡፡
Verse 10
ﮓﮔﮕﮖﮗﮘ
ﮙ
ሰማይም በግልጽ ጭስ የምትመጣበትን ቀን ተጠባበቅ፡፡
Verse 11
ﮚﮛﮜﮝﮞﮟ
ﮠ
ሰዎችን የሚሸፍን (በኾነ ጭስ) ይህ አሳማሚ ቅጣት ነው፡፡
Verse 12
ﮡﮢﮣﮤﮥﮦ
ﮧ
«ጌታችን ሆይ! ከእኛ ላይ ቅጣቱን ግለጥልን፡፡ እኛ አማኞች እንኾናለንና» (ይላሉም)፡፡
Verse 13
(ቅጣቱ በወረደ ጊዜ) ለእነርሱ መግገሰጽ እንዴት ይኖራቸዋል? አስረጅ መልክተኛ የመጣቸው ሲኾን (የካዱም ሲኾኑ)፡፡
Verse 14
ﮰﮱﯓﯔﯕﯖ
ﯗ
ከዚያም ከእርሱ የዞሩ፤ (ከሰው) «የተሰተማረ ዕብድ ነው» ያሉም ሲኾኑ፡፡
Verse 15
እኛ ቅጣቱን ለጥቂት ጊዜ ገላጮች ነን፡፡ እናንተ (ወደ ክህደታችሁ) በእርግጥ ተመላሾች ናችሁ፡፡
Verse 16
ﯠﯡﯢﯣﯤﯥ
ﯦ
ታላቂቱን ብርቱ አያያዝ በምንይዝበት ቀን፤ እኛ ተበቃዮች ነን፡፡
Verse 17
ከእነርሱም በፊት የፈርዖንን ሕዝቦች በእርግጥ ሞከርን፡፡ ክቡር መልእክተኛም መጣላቸው፡፡
Verse 18
«የአላህን ባሮች ወደኔ አድርሱ፡፡ እኔ ለእናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝና፡፡
Verse 19
«በአላህም ላይ አትኩሩ፡፡ እኔ ግልጽ የኾነን አስረጅ ያመጣሁላችሁ ነኝና (በማለት መጣላቸው)፡፡
Verse 20
ﭜﭝﭞﭟﭠﭡ
ﭢ
«እኔም እንዳትወግሩኝ በጌታየና በጌታችሁ ተጠብቂያለሁ፡፡
Verse 21
ﭣﭤﭥﭦﭧ
ﭨ
«በእኔም ባታምኑ ራቁኝ» (ተዉኝ አለ)፡፡
Verse 22
ﭩﭪﭫﭬﭭﭮ
ﭯ
ቀጥሎም (ስለ ዛቱበት) «እነዚህ አመጸኞች ሕዝቦች ናቸው» (አጥፋቸው) ሲል ጌታውን ለመነ፡፡
Verse 23
ﭰﭱﭲﭳﭴ
ﭵ
(ጌታው) «ባሮቼንም ይዘህ በሌሊት ኺድ፡፡ እናንተ የሚከተሉዋችሁ ናችሁና፡፡
Verse 24
«ባሕሩንም የተከፈተ ኾኖ ተወው፡፡ እነርሱ የሚሰጥጠሙ ሰራዊት ናቸውና» (አለው)፡፡
Verse 25
ﭾﭿﮀﮁﮂ
ﮃ
ከአትክልቶችና ከምንጮችም ብዙ ነገሮችን ተዉ፡፡
Verse 26
ﮄﮅﮆ
ﮇ
ከአዝመራዎችም ከመልካም መቀመጫም፡፡
Verse 27
ﮈﮉﮊﮋ
ﮌ
በእርሷ ተደሳቾች ከነበሩባትም ድሎት (ብዙን ነገር ተዉ)፡፡
Verse 28
ﮍﮎﮏﮐﮑ
ﮒ
(ነገሩ) እንደዚሁ ኾነ፡፡ ሌሎችንም ሕዝቦች አወረስናት፡፡
Verse 29
ሰማይና ምድርም በእነርሱ ላይ አላለቀሱም፡፡ የሚቆዩም አልነበሩም፡፡
Verse 30
የእስራኤልንም ልጆች አዋራጅ ከኾነ ስቃይ በእርግጥ አዳንናቸው፡፡
Verse 31
ከፈርዖን፤ እርሱ የኮራ ከወሰን አላፊዎቹ ነበርና፡፡
Verse 32
ﮭﮮﮯﮰﮱﯓ
ﯔ
ከማወቅም ጋር በዓለማት ላይ በእርግጥ መረጥናቸው፡፡
Verse 33
ከታምራቶችም በውስጡ ግልጽ የኾነ ፈተና ያለበትን ሰጠናቸው፡፡
Verse 34
ﯝﯞﯟ
ﯠ
እነዚህ (የመካ ከሓዲዎች) በእርግጥ ይላሉ፡-
Verse 35
እርሷ የፊተኛይቱ ሞታችን እንጅ አይደለችም፡፡ እኛም የምንቀሰቀስ አይደለንም፡፡
Verse 36
ﯪﯫﯬﯭﯮ
ﯯ
እውነተኞችም እንደ ኾናችሁ አባቶቻችንን አምጡልን፡፡
Verse 37
እነርሱ በላጮች ናቸውን ወይስ የቱብበዕ ሕዝቦችና እነዚያ ከእነርሱ በፊት የነበሩት? አጠፋናቸው፡፡ እነርሱ አመጸኞች ነበሩና፡፡
Verse 38
ሰማያትንና ምድርንም በሁለቱ መካከል ያለውንም ሁሉ ቀላጆች ኾነን አልፈጠርንም፡፡
Verse 39
ሁለቱንም በምር እንጅ አልፈጠርናቸውም፡፡ ግን አብዛኞቻቸው አያውቁም፡፡
Verse 40
ﭑﭒﭓﭔﭕ
ﭖ
የመለያው ቀን ለሁሉም ቀጠሯቸው ነው፡፡
Verse 41
ዘመድ ከዘመዱ ምንንም የማይጠቅምበት እነርሱም የማይርረዱበት ቀን ነው፡፡
Verse 42
አላህ ያዘነለት ሰውና ያመነ ብቻ ሲቀር፡፡ (እርሱስ ይርረዳል)፡፡ እርሱ አሸናፊው አዛኙ ነውና፡፡
Verse 43
ﭫﭬﭭ
ﭮ
የዘቁመ ዛፍ
Verse 44
ﭯﭰ
ﭱ
የኀጢኣተኛው ምግብ ነው፡፡
Verse 45
ﭲﭳﭴﭵ
ﭶ
እንደ ዘይት አተላ ነው፡፡ በሆዶች ውስጥ የሚፈላ ሲኾን፡፡
Verse 46
ﭷﭸ
ﭹ
እንደ ገነፈለ ውሃ አፈላል (የሚፈላ ሲኾን)፡፡
Verse 47
ﭺﭻﭼﭽﭾ
ﭿ
ያዙት፤ ወደ ገሀነም መካከልም በኀይል ጎትቱት፡፡
Verse 48
ከዚያም «ከራሱ በላይ ከፈላ ውሃ ስቃይ አንቧቡበት፡፡»
Verse 49
ﮈﮉﮊﮋﮌ
ﮍ
«ቅመስ፤ አንተ አሸናፊው ክብሩ ነህና» (ይባላል)፡፡
Verse 50
ﮎﮏﮐﮑﮒﮓ
ﮔ
«ይህ ያ በእርሱ ትጠራጠሩበት የነበራችሁት ነው» (ይባላሉ)፡፡
Verse 51
ﮕﮖﮗﮘﮙ
ﮚ
ጥንቁቆቹ በእርግጥ በጸጥተኛ መኖሪያ ውስጥ ናቸው፡፡
Verse 52
ﮛﮜﮝ
ﮞ
በአትክልቶችና በምንጮች ውስጥ ናቸው፡፡
Verse 53
ﮟﮠﮡﮢﮣ
ﮤ
ፊት ለፊት የተቅጣጩ ኾነው ከስስ ሐርና ከወፍራም ሐር ይለብሳሉ፡፡
Verse 54
ﮥﮦﮧﮨ
ﮩ
(ነገሩ) እንደዚሁ ነው፤ ዓይናማዎች የኾኑን ነጫጭ ሴቶችም እናጠናዳቸዋለን፡፡
Verse 55
ﮪﮫﮬﮭﮮ
ﮯ
በእርሷም ውስጥ የተማመኑ ኾነው፤ ከፍራፍሬ ሁሉ ያዝዛሉ፡፡
Verse 56
የፊተኛይቱን ሞት እንጅ (ዳግመኛ) በእርሷ ውስጥ ሞትን አይቀምሱም፡፡ የገሀነምንም ቅጣት (አላህ) ጠበቃቸው፡፡
Verse 57
ከጌታህ በኾነ ችሮታ (ጠበቃቸው)፡፡ ይህ እርሱ ታላቅ ዕድል ነው፡፡
Verse 58
ﯦﯧﯨﯩﯪ
ﯫ
(ቁርኣኑን) በቋንቋህም ያገራነው (ሕዝቦችህ) ይገነዘቡ ዘንድ ብቻ ነው፡፡
Verse 59
ﯬﯭﯮ
ﯯ
ተጠባበቅም እነርሱ ተጠባባቂዎች ናቸውና፡፡
تقدم القراءة