سورة القيامة

Sadiq and Sani - Amharic translation

የሱራ القيامة ትርጉም በالأمهرية ከSadiq and Sani - Amharic translation

Sadiq and Sani - Amharic translation

Verse 1


(ነገሩ ከሓዲዎች እንደሚሉት) አይደለም፡፡ በትንሣኤ ቀን እምላለሁ፡፡
Verse 2

(ራሷን) ወቃሽ በኾነች ነፍስም እምላለሁ፡፡ (በእርግጥ ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡

ሰው አጥንቶቹን አለመሰብሰባችንን ያስባልን?

አይደለም ጣቶቹን (ፊት እንደ ነበሩ) በማስተካከል ላይ ቻዮች ስንኾን (እንሰበስባቸዋለን)፡፡

ይልቁንም ሰው በፊቱ ባለው ነገር (በትንሣኤ) ሊያስተባብል ይፈልጋል፡፡
Verse 6

«የትንሣኤው ቀን መቼ ነው?» ሲል ይጠይቃል፡፡
Verse 8

ጨረቃም በጨለመ ጊዜ፡፡
Verse 9

ፀሐይና ጨረቃም በተሰበሰቡ ጊዜ፡፡

«ሰው በዚያ ቀን መሸሻው የት ነው?» ይላል፡፡
Verse 11

ይከልከል፤ ምንም መጠጊያ የለም፡፡
Verse 12

በዚያ ቀን መርጊያው ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡

ሰው በዚያ ቀን ባስቀደመውና ባስቆየው ሁሉ ይነገራል፡፡

በእርግጥም ሰው በነፍሱ ላይ አስረጅ ነው፡፡ (አካሎቹ ይመሰክሩበታል)፡፡
Verse 15

ምክንያቶቹን ሁሉ ቢያመጣም እንኳ (አይሰማም)፡፡

በእርሱ (በቁርኣን ንባብ) ልትቸኩል ምላስህን በእርሱ አታላውስ፡፡
Verse 17

(በልብህ ውስጥ) መሰብሰቡና ማንበቡ በእኛ ላይ ነውና፡፡
Verse 18

ባነበብነውም ጊዜ (ካለቀ በኋላ) ንባቡን ተከተል፡፡
Verse 19

ከዚያም ማብራራቱ በእኛ ላይ ነው፡፡
Verse 20

(ከመጣደፍ) ተከልከል፡፡ ይልቁንም (ሰዎች) ፈጣኒቱን (ዓለም) ትወዳላችሁ፡፡
Verse 21

መጨረሻይቱንም (ዓለም) ትተዋላችሁ፡፡ (አትዘጋጁላትም)፡፡
Verse 22

ፊቶች በዚያ ቀን አብሪዎች ናቸው፡፡
Verse 23

ወደ ጌታቸው ተመልካቾች ናቸው፡፡
Verse 24

ፊቶችም በዚያ ቀን ጨፍጋጊዎች ናቸው፡፡

በርሳቸውም ዐደጋ እንደሚሠራባቸው ያረጋግጣሉ፡፡
Verse 26

ንቁ (ነፍስ) ብሪዎችን በደረሰች ጊዜ፤
Verse 28

(ሕመምተኛው) እርሱ (የሰፈረበት ነገር ከዚህ ዓለም) መልለየት መኾኑን ባረጋገጠም ጊዜ፡፡
Verse 29

ባትም በባት በተጣበቀች ጊዜ፡፡
Verse 30

በዚያ ቀን መነዳቱ ወደ ጌታህ (ፍርድ) ነው፡፡
Verse 32

ግን አስተባበለ፤ (ከእምነት) ዞረም፡፡

ከዚያም እየተንጎባለለ ወደ ቤተሰቡ ኼደ፡፡
Verse 34

የምትጠላውን ነገር (አላህ) ያስከትልህ፡፡ ለአንተ ተገቢህም ነው፡፡
Verse 35

ከዚያም ጥፋት ይጠጋህ ለአንተ የተገባህም ነው፡፡

ከዚያም የረጋ ደም ኾነ (አላህ ሰው አድርጎ) ፈጠረውም፡፡ አስተካከለውም፡፡

ከእርሱም ሁለት ዓይነቶችን ወንድና ሴትን አደረገ፡፡
تقدم القراءة