የሱራ القيامة ትርጉም በالأمهرية ከSadiq and Sani - Amharic translation
Verse 1
ﮊﮋﮌﮍ
ﮎ
(ነገሩ ከሓዲዎች እንደሚሉት) አይደለም፡፡ በትንሣኤ ቀን እምላለሁ፡፡
Verse 2
ﮏﮐﮑﮒ
ﮓ
(ራሷን) ወቃሽ በኾነች ነፍስም እምላለሁ፡፡ (በእርግጥ ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡
Verse 3
ﮔﮕﮖﮗﮘ
ﮙ
ሰው አጥንቶቹን አለመሰብሰባችንን ያስባልን?
Verse 4
ﮚﮛﮜﮝﮞﮟ
ﮠ
አይደለም ጣቶቹን (ፊት እንደ ነበሩ) በማስተካከል ላይ ቻዮች ስንኾን (እንሰበስባቸዋለን)፡፡
Verse 5
ﮡﮢﮣﮤﮥ
ﮦ
ይልቁንም ሰው በፊቱ ባለው ነገር (በትንሣኤ) ሊያስተባብል ይፈልጋል፡፡
Verse 6
ﮧﮨﮩﮪ
ﮫ
«የትንሣኤው ቀን መቼ ነው?» ሲል ይጠይቃል፡፡
Verse 7
ﮬﮭﮮ
ﮯ
ዓይንም በዋለለ ጊዜ፡፡
Verse 8
ﮰﮱ
ﯓ
ጨረቃም በጨለመ ጊዜ፡፡
Verse 9
ﯔﯕﯖ
ﯗ
ፀሐይና ጨረቃም በተሰበሰቡ ጊዜ፡፡
Verse 10
ﯘﯙﯚﯛﯜ
ﯝ
«ሰው በዚያ ቀን መሸሻው የት ነው?» ይላል፡፡
Verse 11
ﯞﯟﯠ
ﯡ
ይከልከል፤ ምንም መጠጊያ የለም፡፡
Verse 12
ﯢﯣﯤﯥ
ﯦ
በዚያ ቀን መርጊያው ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡
Verse 13
ﯧﯨﯩﯪﯫﯬ
ﯭ
ሰው በዚያ ቀን ባስቀደመውና ባስቆየው ሁሉ ይነገራል፡፡
Verse 14
ﯮﯯﯰﯱﯲ
ﯳ
በእርግጥም ሰው በነፍሱ ላይ አስረጅ ነው፡፡ (አካሎቹ ይመሰክሩበታል)፡፡
Verse 15
ﯴﯵﯶ
ﯷ
ምክንያቶቹን ሁሉ ቢያመጣም እንኳ (አይሰማም)፡፡
Verse 16
ﯸﯹﯺﯻﯼﯽ
ﯾ
በእርሱ (በቁርኣን ንባብ) ልትቸኩል ምላስህን በእርሱ አታላውስ፡፡
Verse 17
ﯿﰀﰁﰂ
ﰃ
(በልብህ ውስጥ) መሰብሰቡና ማንበቡ በእኛ ላይ ነውና፡፡
Verse 18
ﰄﰅﰆﰇ
ﰈ
ባነበብነውም ጊዜ (ካለቀ በኋላ) ንባቡን ተከተል፡፡
Verse 19
ﰉﰊﰋﰌ
ﰍ
ከዚያም ማብራራቱ በእኛ ላይ ነው፡፡
Verse 20
ﭑﭒﭓﭔ
ﭕ
(ከመጣደፍ) ተከልከል፡፡ ይልቁንም (ሰዎች) ፈጣኒቱን (ዓለም) ትወዳላችሁ፡፡
Verse 21
ﭖﭗ
ﭘ
መጨረሻይቱንም (ዓለም) ትተዋላችሁ፡፡ (አትዘጋጁላትም)፡፡
Verse 22
ﭙﭚﭛ
ﭜ
ፊቶች በዚያ ቀን አብሪዎች ናቸው፡፡
Verse 23
ﭝﭞﭟ
ﭠ
ወደ ጌታቸው ተመልካቾች ናቸው፡፡
Verse 24
ﭡﭢﭣ
ﭤ
ፊቶችም በዚያ ቀን ጨፍጋጊዎች ናቸው፡፡
Verse 25
ﭥﭦﭧﭨﭩ
ﭪ
በርሳቸውም ዐደጋ እንደሚሠራባቸው ያረጋግጣሉ፡፡
Verse 26
ﭫﭬﭭﭮ
ﭯ
ንቁ (ነፍስ) ብሪዎችን በደረሰች ጊዜ፤
Verse 27
ﭰﭱﭲﭳ
ﭴ
«አሻሪው ማነው?» በተባለም ጊዜ፡፡
Verse 28
ﭵﭶﭷ
ﭸ
(ሕመምተኛው) እርሱ (የሰፈረበት ነገር ከዚህ ዓለም) መልለየት መኾኑን ባረጋገጠም ጊዜ፡፡
Verse 29
ﭹﭺﭻ
ﭼ
ባትም በባት በተጣበቀች ጊዜ፡፡
Verse 30
ﭽﭾﭿﮀ
ﮁ
በዚያ ቀን መነዳቱ ወደ ጌታህ (ፍርድ) ነው፡፡
Verse 31
ﮂﮃﮄﮅ
ﮆ
አላመነምም አልሰገደምም፡፡
Verse 32
ﮇﮈﮉ
ﮊ
ግን አስተባበለ፤ (ከእምነት) ዞረም፡፡
Verse 33
ﮋﮌﮍﮎﮏ
ﮐ
ከዚያም እየተንጎባለለ ወደ ቤተሰቡ ኼደ፡፡
Verse 34
ﮑﮒﮓ
ﮔ
የምትጠላውን ነገር (አላህ) ያስከትልህ፡፡ ለአንተ ተገቢህም ነው፡፡
Verse 35
ﮕﮖﮗﮘ
ﮙ
ከዚያም ጥፋት ይጠጋህ ለአንተ የተገባህም ነው፡፡
Verse 36
ﮚﮛﮜﮝﮞ
ﮟ
ሰው ስድ ኾኖ መትተውን ይጠረጥራልን?
Verse 37
ﮠﮡﮢﮣﮤﮥ
ﮦ
የሚፈሰስ ከኾነ የፍትወት ጠብታ አልነበረምን?
Verse 38
ﮧﮨﮩﮪﮫ
ﮬ
ከዚያም የረጋ ደም ኾነ (አላህ ሰው አድርጎ) ፈጠረውም፡፡ አስተካከለውም፡፡
Verse 39
ﮭﮮﮯﮰﮱ
ﯓ
ከእርሱም ሁለት ዓይነቶችን ወንድና ሴትን አደረገ፡፡
Verse 40
ይህ (ጌታ) ሙታንን ሕያው በማድረግ ላይ ቻይ አይደለምን?
تقدم القراءة