surah.translation .


ያንን በምርመራው የሚያስተባብለውን አየህን? (ዐወቅከውን?)

ይህም ያ የቲምን በኀይል የሚገፈትረው፤

ድኻንም በማብላት ላይ የማያግባባው ሰው ነው፡፡

ወዮላቸው ለሰጋጆች፡፡

ለእነዚያ እነርሱ ከስግደታቸው ዘንጊዎች ለኾኑት፤ (ሰጋጆች)፡፡

ለእነዚያ እነርሱ ይዩልኝ ባዮች ለኾኑት፡፡

የዕቃ ትውስትንም (ሰዎችን) የሚከለክሉ ለኾኑት (ወዮላቸው)፡፡