سورة المرسلات

Sadiq and Sani - Amharic translation

የሱራ المرسلات ትርጉም በالأمهرية ከSadiq and Sani - Amharic translation

Sadiq and Sani - Amharic translation

Verse 1


ተከታታይ ኾነው በተላኩት፣
Verse 2

በኀይል መንፈስን ነፋሾች በኾኑትም፣
Verse 3

መበተንን በታኞች በኾኑትም፤ (ነፋሶች)፣
Verse 4

መለየትን ለይዎች በኾኑትም፣
Verse 5

መገሠጫን (ወደ ነቢያት) ጣይዎች በኾኑትም፣
Verse 6

ምክንያትን ለማስወገድ ወይም ለማስፈራራት (ጣይዎች በኾኑት መላእክት) እምላለሁ፡፡
Verse 7

ያ የምትስፈራሩበት (ትንሣኤ) በእርግጥ ኋኝ ነው፡፡
Verse 8

ከዋክብትም (ብርሃንዋ) በታበሰች ጊዜ፡፡
Verse 10

ጋራዎችም በተንኮተኮቱ ጊዜ፡፡
Verse 11

መልክተኞቹም ወቅት በተደረገላቸው ጊዜ፡፡
Verse 12

ለየትኛው ቀን ተቀጠሩ (የሚባል ሲኾን)፤
Verse 13

ለመለያው ቀን (በተባለ ጊዜ፤ በፍጡሮች መካከል ይፈረዳል)፡፡

የመለያውም ቀን ምን እንደኾነ ምን አሳወቀህ?
Verse 15

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
Verse 16

የፊተኞቹን (ሕዝቦች) አላጠፋንምን?
Verse 17

ከዚያም የኋለኞቹን እናስከትላቸዋለን፡፡
Verse 18

በአመጸኞች ሁሉ እንደዚሁ እንሠራለን፡፡
Verse 19

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
Verse 21

በተጠበቀ መርጊያ ውስጥም (በማሕፀን) አደረግነው፡፡
Verse 22

እስከ ታወቀ ልክ ድረስ፡፡ መጠንነውም፤ ምን ያማርንም
Verse 24

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
Verse 26

ሕያዋን ኾናችሁ ሙታንም ኾናችሁ፡፡

በውስጧም ከፍተኛዎችን ተራራዎች አደረግን፡፡ ጣፋጭ ውሃንም አጠጣናችሁ፡፡
Verse 28

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

«ወደዚያ በእርሱ ታስተባብሉ ወደ ነበራችሁት (ቅጣት) አዝግሙ፡፡

«ባለ ሦስት ቅርንጫፎች ወደ ኾነው ጥላ አዝግሙ፤» (ይባላሉ)፡፡

አጠላይ ያልኾነ ከእሳቱም ላንቃ የማያድን ወደ ኾነው (አዝግሙ)፡፡
Verse 32

እርሷ እንደ ታላላቅ ሕንጻ የኾኑን ቃንቄዎች ትወረውራለች፡፡
Verse 33

(ቃንቄውም) ልክ ዳለቻዎች ግመሎችን ይመስላል፡፡
Verse 34

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
Verse 36

ይቅርታም ይጠይቁ ዘንድ፤ ለእነርሱ አይፈቀድላቸውም፡፡
Verse 37

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

ይህ መለያው ቀን ነው፡፡ እናንተንም የፊተኞቹንም ሰብሰብናችሁ፡፡

ለናንተም (ለማምለጥ) ብልሃት እንዳላችሁ ተተናኮሉኝ፡፡
Verse 40

ላስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

ጥንቁቆቹ በጥላዎችና በምንጮች ውስጥ ናቸው፡፡
Verse 42

ከሚከጅሉትም ሁሉ በፍራፍሬዎች ውስጥ ናቸው፡፡

«ትሠሩት በነበራችሁት ዋጋ የምትደሰቱ ኾናችሁ ብሉ፣ ጠጡም፤» (ይባላሉ)፡፡
Verse 44

እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን ሁሉ እንመነዳለን፡፡
Verse 45

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

ብሉ፤ ጥቂትንም (ጊዜ) ተጠቀሙ፡፡ እናንተ አመጸኞች ናችሁና፡፡
Verse 47

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
Verse 49

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
Verse 50

ከእርሱም ሌላ በየትኛው ንግግር ያምናሉ?
تقدم القراءة