سورة الواقعة

Sadiq and Sani - Amharic translation

የሱራ الواقعة ትርጉም በالأمهرية ከSadiq and Sani - Amharic translation

Sadiq and Sani - Amharic translation

Verse 2

ለመውደቋ አስተባባይ (ነፍስ) የለችም፡፡
Verse 3

ዝቅ አድራጊና ከፍ አድራጊ ናት፡፡
Verse 5

ተራራዎችም መፍፈርፈርን በተፈረፈሩ ጊዜ (እንደተፈጨ ዱቄት በኾኑ ጊዜ)፡፡
Verse 7

ሦስት ዓይነቶችም በኾናችሁ ጊዜ (ታዋርዳለች፤ ታነሳለችም)፡፡

የቀኝ ጓዶችም ምን (የተከበሩ) የቀኝ ጓዶች ናቸው፡፡

የግራ ጓዶችም ምን (የተዋረዱ) የግራ ጓዶች ናቸው፡፡
Verse 10

(ለበጎ ሥራ) ቀዳሚዎቹም (ለገነት) ቀዳሚዎች ናቸው፡፡
Verse 11

እነዚያ ባለሟሎቹ ናቸው፡፡
Verse 12

በመጠቀሚያ ገነቶች ውስጥ ሲኾኑ፡፡
Verse 13

ከፊተኞቹ ብዙ ጭፍሮች ናቸው፡፡
Verse 14

ከኋለኞቹም ጥቂቶች ናቸው፡፡
Verse 15

በተታቱ አልጋዎች ላይ ይኾናሉ፡፡
Verse 16

በእርሷ ላይ የተመቻቹና ፊት ለፊት የተቅጣጩ ሲኾኑ፡፡
Verse 17

በእነርሱ ላይ ሁል ጊዜ የማያረጁ ወጣቶች ልጆች ይዘዋወራሉ፡፡

ከጠጅ ምንጭም በብርጭቆዎችና በኩስኩስቶች በጽዋም (በእነርሱ ላይ ይዝዞራሉ)፡፡

ከእርሷ የራስ ምታት አያገኛቸውም፤ አይሰክሩምም፡፡
Verse 20

ከሚመርጡትም ዓይነት በእሸቶች፡፡
Verse 21

ከሚሹትም በኾነ የበራሪ ሥጋ (ይዞሩባቸዋል)፡፡
Verse 22

ዓይናማዎች የኾኑ ነጫጭ ቆንጆዎችም አሏቸው፡፡
Verse 23

ልክ እንደተሸፈነ ሉል መሰሎች የኾኑ፡፡
Verse 24

በዚያ ይሠሩት በነበሩት ምክንያት ዋጋ ይኾን ዘንድ (ይህንን አደረግንላቸው)፡፡

በውስጥዋ ውድቅ ንግግርንና መውወንጀልን አይሰሙም፡፡
Verse 28

በተቀፈቀፈ (እሾህ በሌለው) ቁርቁራ ውስጥ ናቸው፡፡
Verse 29

(ፍሬው) በተነባበረ በሙዝ ዛፍም፡፡
Verse 30

በተዘረጋ ጥላ ሥርም፡፡
Verse 31

በሚንቧቧ ውሃ አጠገብም፡፡
Verse 32

ብዙ (ዓይነት) በኾኑ ፍራፍሬዎችም፡፡
Verse 33

የማትቋረጥም የማትከለከልም የኾነች፡፡
Verse 34

ከፍ በተደረጉ ምንጣፎችም (ሴቶችም መካከል)፡፡
Verse 35

እኛ አዲስ ፍጥረት አድርገን (ለእነርሱ) ፈጠርናቸው፡፡
Verse 36

ደናግሎችም አደረግናቸው፡፡
Verse 37

ለባሎቻቸው ተሽሞርሟሪዎች እኩያዎች (አደረግናቸው)፡፡
Verse 38

ለቀኝ ጓዶች (አዘጋጀናቸው)፡፡
Verse 39

ከፊተኞቹ ብዙ ጭፍሮች ናቸው፡፡
Verse 40

ከኋለኞቹም ብዙ ጭፍሮች ናቸው፡፡

የግራ ጓደኞችም ምንኛ (የተዋረዱ) የግራ ጓዶች! ናቸው፡፡
Verse 42

በመርዛም ነፋስ በጣም በፈላ ውሃም ውስጥ ናቸው፡፡
Verse 43

ከጥቁር ጭስም በኾነ ጥላ ውስጥ፡፡

በታላቅ ኀጢአትም ላይ ይዘወትሩ ነበሩና፡፡

ይሉም ነበሩ፡- «በሞትንና ዐፈር፣ ዐጥንቶችም በኾን ጊዜ እኛ በእርግጥ የምንቀሰቀስ ነን?
Verse 48

«የፊተኞቹ አባቶቻችንም?»

«በተወሰነ ቀን ቀጠሮ በእርግጥ ተሰብሳቢዎች ናቸው፡፡

«ከዚያም እናንተ ጠማሞች አስተባባዮች ሆይ!
Verse 53

«ከእርሷም ሆዶቻችሁን ሞይዎች ናችሁ፡፡
Verse 54

«በእርሱ ላይም ከፈላ ውሃ ጠጪዎች ናችሁ፡፡
Verse 55

«የተጠሙንም ግመሎች አጠጣጥ ብጤ ጠጪዎች ናችሁ፡፡»
Verse 56

ይህ በፍርዱ ቀን መስተንግዷቸው ነው፡፡
Verse 58

(በማኅፀኖች) የምታፈሱትን አያችሁን?

እናንተ ትፈጥሩታላችሁን? ወይስ እኛ ፈጣሪዎቹን ነን?

እኛ ሞትን (ጊዜውን) በመካከላችሁ ወሰንን፡፡ እኛም ተሸናፊዎች አይደለንም፡፡

ብጤዎቻችሁን በመለወጥና በዚያ በማታውቁትም (ቅርጽ) እናንተን በመፍጠር ላይ (አንሸነፍም)፡፡

የፊተኛይቱንም አፈጣጠር በእርግጥ ዐውቃችኋል፡፡ አትገነዘቡምን?

እናንተ ታበቅሉታላችሁን? ወይስ እኛ አብቃዮቹ ነን?

ብነሻ ኖሮ ደረቅ ስብርብር ባደረግነውና የምትደነቁም በኾናችሁ ነበር፡፡
Verse 66

«እኛ በዕዳ ተያዦች ነን፡፡
Verse 67

«በእርግጥም እኛ (ከመጠቀም) የተከለከልን ነን» (ትሉ ነበር)፡፡
Verse 68

ያንንም የምትጠጡትን ውሃ አየችሁን?

እናንተ ከደመናው አወረዳችሁትን? ወይስ እኛ አውራጆቹ ነን?

ብንሻ ኖሮ መርጋጋ ባደረግነው ነበር፡፡ አታመሰግኑምን?
Verse 71

ያቺንም የምትሰብቋትን እሳት አያችሁን?

እናንተ ዛፏን ፈጠራችሁን? ወይስ እኛ ፈጣሪዎችዋ ነን?

እኛ (ለገሀናም) ማስታወሻ ለመንገደኞችም መጠቀሚያ አደረግናት፡፡
Verse 77

እርሱ የከበረ ቁርኣን ነው፡፡
Verse 78

በተጠበቀ መጽሐፍ ውስጥ ነው፡፡
Verse 79

የተጥራሩት እንጅ ሌላ አይነካውም፡፡
Verse 81

በዚህ ንግግር እናንተ ቸልተኞች ናችሁን?
Verse 82

ሲሳያችሁንም (ዝናምን) እናንተ የምታስተባብሉት ታደርጋላችሁን?
Verse 84

እናንተ ያን ጊዜ የምታዩ ስትኾኑ፡፡

እኛም ግን አታዩም እንጅ ከእናንተ ይልቅ ወደእርሱ የቀረብን ስንኾን፡፡
Verse 87

እውነተኞች እንደ ኾናችሁ (ነፍሲቱን ወደ አካሉ) ለምን አትመልሷትም፡፡
Verse 89

(ለእርሱ) ዕረፍት፣ መልካም ሲሳይም፣ የመጠቀሚያ ገነትም አልለው፡፡

ከቀኝ ጓዶች ስለ ኾንክ ላንተ ሰላም አልለህ (ይባላል)፡፡
Verse 93

ከፈላ ውሃ የኾነ መስተንግዶ አልለው፡፡
Verse 94

በገሀነም መቃጠልም (አልለው)፡፡
تقدم القراءة