سورة النجم

Sadiq and Sani - Amharic translation

የሱራ النجم ትርጉም በالأمهرية ከSadiq and Sani - Amharic translation

Sadiq and Sani - Amharic translation

Verse 1


በኮከብ እምላለሁ በወደቀ (በገባ) ጊዜ፡፡

ነቢያችሁ (ሙሐመድ) አልተሳሳተም፤ አልጠመመምም፡፡

እርሱ (ንግግሩ) የሚወርረድ ራእይ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡
Verse 5

ኀይሎቹ ብርቱው (መልአክ) አስተማረው፡፡
Verse 6

የዕውቀት ባለቤት የኾነው (አስተማረው፤ በተፈጥሮ ቅርጹ ኾኖ በአየር ላይ) ተደላደለም፡፡
Verse 7

እርሱ በላይኛው አድማስ ኾኖ፡፡

(ከእርሱ) የሁለት ደጋኖች ጫፍ ያህል ወይም (ከዚህ) ይበልጥ የቀረበ ኾነም፡፡

ወደ ባሪያውም (አላህ) ያወረደውን አወረደ፡፡
Verse 12

ታዲያ በሚያየው ላይ ትከራከሩታላችሁን?
Verse 13

በሌላይቱም መውረድ ጊዜ በእርግጥ አይቶታል፡፡
Verse 14

በመጨረሻይቱ ቁርቁራ አጠገብ፤
Verse 15

እርሷ ዘንድ መኖሪያይቱ ገነት ያለች ስትኾን፡፡

ቁርቁራይቱን የሚሸፍን ነገር በሚሸፍናት ጊዜ (አየው)፡፡

ዓይኑ (ካየው) አልተዘነበለም፡፡ ወሰንም አላለፈም፡፡
Verse 19

አል-ላትንና አል-ዑዛን አያችሁን?
Verse 20

ሦስተኛይቱንም አነስተኛዋን መናትን (አያችሁን? የምትግገዟቸው ኃይል አላቸውን?)
Verse 21

ለእናንተ ወንድ ለእርሱም ሴት (ልጅ) ይኖራልን?
Verse 22

ይህቺ ያን ጊዜ አድላዊ ክፍያ ናት፡፡

እነርሱ እናንተና አባቶቻችሁ (አማልክት ብላችሁ) የጠራችኋቸው ስሞች ብቻ እንጅ ምንም አይደሉም፡፡ አላህ በእርሷ (መግገዛት) ምንም ማስረጃ አላወረደም፡፡ ከጌታቸውም መምሪያ የመጣላቸው ሲኾኑ ጥርጣሬንና ነፍሶች የሚዘነበሉበትን እንጅ ሌላ አይከተሉም፡፡
Verse 25

መጨረሻይቱም መጀመሪያይቱም (ዓለም) የአላህ ብቻ ናቸው፡፡

እነዚያ በመጨረሻይቱ ዓለም የማያምኑት መላእክትን በሴት አጠራር ይጠራሉ፡፡

ከግሣጼያችንም (ከቁርኣን) ከሸሸና አነስተኛይቱን ሕይወት እንጅ ሌላን ከማይሻ ሰው ዙር (ተወው)፡፡

ይህ (አነስተኛይቱን ሕይወት መምረጥ) ከዕውቀት ድካቸው ነው፡፡ ጌታህ እርሱ ከመንገዱ የተሳሳተውን በእርግጥ ዐዋቂ ነው፡፡ እርሱም የቀናውን ሰው ዐዋቂ ነው፡፡

በሰማያት ያለውና በምድር ያለው ሁሉ የአላህ ነው፡፡ እነዚያን ያጠፉትን በሠሩት ሊቀጣ እነዚያን ያሳመሩትንም በመልካሚቱ (ገነት) ሊመነዳ (የጠመመውንና የቀናውን ያውቃል)፡፡

(እነርሱ) እነዚያ የኃጢኣትን ታላለቆችና አስጸያፊዎቹን የሚርቁ ናቸው፡፡ ግን ትናንሾቹ የሚማሩ ናቸው፡፡ ጌታህ ምሕረተ ሰፊ ነውና፡፡ ከምድር በፈጠራችሁ ጊዜ እናንተም በእናቶቻችሁ ሆዶች ውስጥ ሽሎች በኾናችሁ ጊዜ እርሱ በናንተ (ኹነታ) ዐዋቂ ነው፡፡ ነፍሶቻችሁንም አታወድሱ እርሱ የሚፈራውን ሰው ዐዋቂ ነው፡፡
Verse 33

ያንን (ከእምነት) የዞረውን አየህን?
Verse 34

ጥቂትን የሰጠውንና ያቋረጠውንም (አየህን?)

የሩቁ ምስጢር ዕውቀት እርሱ ዘንድ አልለን? ስለዚህ እርሱ ያያልን?

ይልቁንም በዚያ በሙሳ ጽሑፎች ውስጥ ባለው ነገር አልተነገረምን?
Verse 37

በዚያም (የታዘዘውን) በፈጸመው በኢብራሂም (ጽሑፎች ውስጥ ባለው አልተነገረምን?)

(እርሱም ኃጢያት) ተሸካሚ ነፍስ የሌላይቱን ነፍስ ኃጢኣት አትሸከምም፡፡
Verse 41

ከዚያም ሙሉውን ምንዳ ይመነዳዋል፡፡
Verse 43

እነሆ እርሱም አስሳቀ፣ አስለቀሰም፡፡

እርሱም ሁለቱን ዓይነቶች ወንድንና ሴትን ፈጠረ፡፡
Verse 46

ከፍትወት ጠብታ (በማህጸን ውስጥ) በምትፈሰስ ጊዜ፡፡
Verse 47

የኋለኛይቱም ማስነሳት በእርሱ ላይ ነው፡፡
Verse 48

እነሆ እርሱም አከበረ፣ ጥሪተኛም አደረገ፡፡
Verse 50

እነሆ እርሱም የፊተኛይቱን ዓድ አጥፍቷል፡፡
Verse 51

ሰሙድንም (አጥፍቷል)፤ አላስቀረምም፡፡

በፊትም የኑሕን ሕዝቦች (አጥፍቷል)፡፡ እነርሱ በጣም በደለኞችና እጅግ የጠመሙ እነርሱ ነበሩና፡፡
Verse 53

የተገለበጠችውንም ከተማ ደፋ፡፡
Verse 55

ከጌታህም ጸጋዎች በየትኛው ትጠራጠራለህ?

ይህ ከፊተኞቹ አስፈራሪዎች (ጎሳ) የኾነ አስፈራሪ ነው፡፡
Verse 57

ቀራቢይቱ (ኅልፈተ ዓለም) ቀረበች፡፡
Verse 60

ትስቃላችሁምን? አታለቅሱምን?
Verse 61

እናንተም ዘንጊዎች ናችሁ፡፡
تقدم القراءة