የሱራ النجم ትርጉም በالأمهرية ከالترجمة الأمهرية
Verse 1
ﭑﭒﭓ
ﭔ
በኮከብ እምላለሁ በወደቀ (በገባ) ጊዜ፡፡
Verse 2
ﭕﭖﭗﭘﭙ
ﭚ
ነቢያችሁ (ሙሐመድ) አልተሳሳተም፤ አልጠመመምም፡፡
Verse 3
ﭛﭜﭝﭞ
ﭟ
ከልብ ወለድም አይናገርም፡፡
Verse 4
ﭠﭡﭢﭣﭤ
ﭥ
እርሱ (ንግግሩ) የሚወርረድ ራእይ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡
Verse 5
ﭦﭧﭨ
ﭩ
ኀይሎቹ ብርቱው (መልአክ) አስተማረው፡፡
Verse 6
ﭪﭫﭬ
ﭭ
የዕውቀት ባለቤት የኾነው (አስተማረው፤ በተፈጥሮ ቅርጹ ኾኖ በአየር ላይ) ተደላደለም፡፡
Verse 7
ﭮﭯﭰ
ﭱ
እርሱ በላይኛው አድማስ ኾኖ፡፡
Verse 8
ﭲﭳﭴ
ﭵ
ከዚያም ቀረበ፤ ወረደም፡፡
Verse 9
ﭶﭷﭸﭹﭺ
ﭻ
(ከእርሱ) የሁለት ደጋኖች ጫፍ ያህል ወይም (ከዚህ) ይበልጥ የቀረበ ኾነም፡፡
Verse 10
ﭼﭽﭾﭿﮀ
ﮁ
ወደ ባሪያውም (አላህ) ያወረደውን አወረደ፡፡
Verse 11
ﮂﮃﮄﮅﮆ
ﮇ
(ነቢዩም በዓይኑ) ያየውን ልቡ አልዋሸም፡፡
Verse 12
ﮈﮉﮊﮋ
ﮌ
ታዲያ በሚያየው ላይ ትከራከሩታላችሁን?
Verse 13
ﮍﮎﮏﮐ
ﮑ
በሌላይቱም መውረድ ጊዜ በእርግጥ አይቶታል፡፡
Verse 14
ﮒﮓﮔ
ﮕ
በመጨረሻይቱ ቁርቁራ አጠገብ፤
Verse 15
ﮖﮗﮘ
ﮙ
እርሷ ዘንድ መኖሪያይቱ ገነት ያለች ስትኾን፡፡
Verse 16
ﮚﮛﮜﮝﮞ
ﮟ
ቁርቁራይቱን የሚሸፍን ነገር በሚሸፍናት ጊዜ (አየው)፡፡
Verse 17
ﮠﮡﮢﮣﮤ
ﮥ
ዓይኑ (ካየው) አልተዘነበለም፡፡ ወሰንም አላለፈም፡፡
Verse 18
ﮦﮧﮨﮩﮪﮫ
ﮬ
ከጌታው ታምራቶች ታላላቆቹን በእርግጥ አየ፡፡
Verse 19
ﮭﮮﮯ
ﮰ
አል-ላትንና አል-ዑዛን አያችሁን?
Verse 20
ﮱﯓﯔ
ﯕ
ሦስተኛይቱንም አነስተኛዋን መናትን (አያችሁን? የምትግገዟቸው ኃይል አላቸውን?)
Verse 21
ﯖﯗﯘﯙ
ﯚ
ለእናንተ ወንድ ለእርሱም ሴት (ልጅ) ይኖራልን?
Verse 22
ﯛﯜﯝﯞ
ﯟ
ይህቺ ያን ጊዜ አድላዊ ክፍያ ናት፡፡
Verse 23
እነርሱ እናንተና አባቶቻችሁ (አማልክት ብላችሁ) የጠራችኋቸው ስሞች ብቻ እንጅ ምንም አይደሉም፡፡ አላህ በእርሷ (መግገዛት) ምንም ማስረጃ አላወረደም፡፡ ከጌታቸውም መምሪያ የመጣላቸው ሲኾኑ ጥርጣሬንና ነፍሶች የሚዘነበሉበትን እንጅ ሌላ አይከተሉም፡፡
Verse 24
ﯼﯽﯾﯿ
ﰀ
ለሰው የተመኘው ሁሉ አለውን?
Verse 25
ﰁﰂﰃ
ﰄ
መጨረሻይቱም መጀመሪያይቱም (ዓለም) የአላህ ብቻ ናቸው፡፡
Verse 26
በሰማያት ውስጥ ካለ መልአክም ብዙዎች (ሊማለዱለት) ለሚሻውና ለሚወደው ሰው ከፈቀደ በኋላ ቢኾን እንጅ ምልጃቸው ምንም አትጠቅምም፡፡
Verse 27
እነዚያ በመጨረሻይቱ ዓለም የማያምኑት መላእክትን በሴት አጠራር ይጠራሉ፡፡
Verse 28
ለእነርሱም በእርሱ ምንም ዕውቀት የላቸውም፡፡ ጥርጣሬን እንጅ ሌላን አይከተሉም፡፡ ጥርጣሬም ከእውነት ምንም አያብቃቃም፡፡
Verse 29
ከግሣጼያችንም (ከቁርኣን) ከሸሸና አነስተኛይቱን ሕይወት እንጅ ሌላን ከማይሻ ሰው ዙር (ተወው)፡፡
Verse 30
ይህ (አነስተኛይቱን ሕይወት መምረጥ) ከዕውቀት ድካቸው ነው፡፡ ጌታህ እርሱ ከመንገዱ የተሳሳተውን በእርግጥ ዐዋቂ ነው፡፡ እርሱም የቀናውን ሰው ዐዋቂ ነው፡፡
Verse 31
በሰማያት ያለውና በምድር ያለው ሁሉ የአላህ ነው፡፡ እነዚያን ያጠፉትን በሠሩት ሊቀጣ እነዚያን ያሳመሩትንም በመልካሚቱ (ገነት) ሊመነዳ (የጠመመውንና የቀናውን ያውቃል)፡፡
Verse 32
(እነርሱ) እነዚያ የኃጢኣትን ታላለቆችና አስጸያፊዎቹን የሚርቁ ናቸው፡፡ ግን ትናንሾቹ የሚማሩ ናቸው፡፡ ጌታህ ምሕረተ ሰፊ ነውና፡፡ ከምድር በፈጠራችሁ ጊዜ እናንተም በእናቶቻችሁ ሆዶች ውስጥ ሽሎች በኾናችሁ ጊዜ እርሱ በናንተ (ኹነታ) ዐዋቂ ነው፡፡ ነፍሶቻችሁንም አታወድሱ እርሱ የሚፈራውን ሰው ዐዋቂ ነው፡፡
Verse 33
ﯢﯣﯤ
ﯥ
ያንን (ከእምነት) የዞረውን አየህን?
Verse 34
ﯦﯧﯨ
ﯩ
ጥቂትን የሰጠውንና ያቋረጠውንም (አየህን?)
Verse 35
ﯪﯫﯬﯭﯮ
ﯯ
የሩቁ ምስጢር ዕውቀት እርሱ ዘንድ አልለን? ስለዚህ እርሱ ያያልን?
Verse 36
ይልቁንም በዚያ በሙሳ ጽሑፎች ውስጥ ባለው ነገር አልተነገረምን?
Verse 37
ﯸﯹﯺ
ﯻ
በዚያም (የታዘዘውን) በፈጸመው በኢብራሂም (ጽሑፎች ውስጥ ባለው አልተነገረምን?)
Verse 38
ﯼﯽﯾﯿﰀ
ﰁ
(እርሱም ኃጢያት) ተሸካሚ ነፍስ የሌላይቱን ነፍስ ኃጢኣት አትሸከምም፡፡
Verse 39
ﰂﰃﰄﰅﰆﰇ
ﰈ
ለሰውም ሁሉ የሠራው እንጅ ሌላ የለውም፡፡
Verse 40
ﰉﰊﰋﰌ
ﰍ
ሥራውም ሁሉ ወደ ፊት ይታያል፡፡
Verse 41
ﰎﰏﰐﰑ
ﰒ
ከዚያም ሙሉውን ምንዳ ይመነዳዋል፡፡
Verse 42
ﰓﰔﰕﰖ
ﰗ
መጨረሻውም ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡
Verse 43
ﰘﰙﰚﰛ
ﰜ
እነሆ እርሱም አስሳቀ፣ አስለቀሰም፡፡
Verse 44
ﰝﰞﰟﰠ
ﰡ
እነሆ እርሱም ገደለ፣ አስነሳም፡፡
Verse 45
ﭑﭒﭓﭔﭕ
ﭖ
እርሱም ሁለቱን ዓይነቶች ወንድንና ሴትን ፈጠረ፡፡
Verse 46
ﭗﭘﭙﭚ
ﭛ
ከፍትወት ጠብታ (በማህጸን ውስጥ) በምትፈሰስ ጊዜ፡፡
Verse 47
ﭜﭝﭞﭟ
ﭠ
የኋለኛይቱም ማስነሳት በእርሱ ላይ ነው፡፡
Verse 48
ﭡﭢﭣﭤ
ﭥ
እነሆ እርሱም አከበረ፣ ጥሪተኛም አደረገ፡፡
Verse 49
ﭦﭧﭨﭩ
ﭪ
እነሆ እርሱም የሺዕራ ጌታ ነው፡፡
Verse 50
ﭫﭬﭭﭮ
ﭯ
እነሆ እርሱም የፊተኛይቱን ዓድ አጥፍቷል፡፡
Verse 51
ﭰﭱﭲ
ﭳ
ሰሙድንም (አጥፍቷል)፤ አላስቀረምም፡፡
Verse 52
በፊትም የኑሕን ሕዝቦች (አጥፍቷል)፡፡ እነርሱ በጣም በደለኞችና እጅግ የጠመሙ እነርሱ ነበሩና፡፡
Verse 53
ﭿﮀ
ﮁ
የተገለበጠችውንም ከተማ ደፋ፡፡
Verse 54
ﮂﮃﮄ
ﮅ
ያለበሳትንም አለበሳት፡፡
Verse 55
ﮆﮇﮈﮉ
ﮊ
ከጌታህም ጸጋዎች በየትኛው ትጠራጠራለህ?
Verse 56
ﮋﮌﮍﮎﮏ
ﮐ
ይህ ከፊተኞቹ አስፈራሪዎች (ጎሳ) የኾነ አስፈራሪ ነው፡፡
Verse 57
ﮑﮒ
ﮓ
ቀራቢይቱ (ኅልፈተ ዓለም) ቀረበች፡፡
Verse 58
ﮔﮕﮖﮗﮘﮙ
ﮚ
ለእርሷ ከአላህ ሌላ ገላጭ የላትም፡፡
Verse 59
ﮛﮜﮝﮞ
ﮟ
ከዚህ ንግግር ትደነቃላችሁን?
Verse 60
ﮠﮡﮢ
ﮣ
ትስቃላችሁምን? አታለቅሱምን?
Verse 61
ﮤﮥ
ﮦ
እናንተም ዘንጊዎች ናችሁ፡፡
Verse 62
ﮧﮨﮩﮪ
ﮫ
ለአላህም ስገዱ ተገዙትም፡፡
تقدم القراءة