سورة النجم

الترجمة الأمهرية

የሱራ النجم ትርጉም በالأمهرية ከالترجمة الأمهرية

الترجمة الأمهرية

Verse 1
በኮከብ እምላለሁ በወደቀ (በገባ) ጊዜ፡፡
ነቢያችሁ (ሙሐመድ) አልተሳሳተም፤ አልጠመመምም፡፡
እርሱ (ንግግሩ) የሚወርረድ ራእይ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡
Verse 5
ኀይሎቹ ብርቱው (መልአክ) አስተማረው፡፡
Verse 6
የዕውቀት ባለቤት የኾነው (አስተማረው፤ በተፈጥሮ ቅርጹ ኾኖ በአየር ላይ) ተደላደለም፡፡
Verse 7
እርሱ በላይኛው አድማስ ኾኖ፡፡
(ከእርሱ) የሁለት ደጋኖች ጫፍ ያህል ወይም (ከዚህ) ይበልጥ የቀረበ ኾነም፡፡
ወደ ባሪያውም (አላህ) ያወረደውን አወረደ፡፡
Verse 12
ታዲያ በሚያየው ላይ ትከራከሩታላችሁን?
Verse 13
በሌላይቱም መውረድ ጊዜ በእርግጥ አይቶታል፡፡
Verse 14
በመጨረሻይቱ ቁርቁራ አጠገብ፤
Verse 15
እርሷ ዘንድ መኖሪያይቱ ገነት ያለች ስትኾን፡፡
ቁርቁራይቱን የሚሸፍን ነገር በሚሸፍናት ጊዜ (አየው)፡፡
ዓይኑ (ካየው) አልተዘነበለም፡፡ ወሰንም አላለፈም፡፡
Verse 19
አል-ላትንና አል-ዑዛን አያችሁን?
Verse 20
ሦስተኛይቱንም አነስተኛዋን መናትን (አያችሁን? የምትግገዟቸው ኃይል አላቸውን?)
Verse 21
ለእናንተ ወንድ ለእርሱም ሴት (ልጅ) ይኖራልን?
Verse 22
ይህቺ ያን ጊዜ አድላዊ ክፍያ ናት፡፡
እነርሱ እናንተና አባቶቻችሁ (አማልክት ብላችሁ) የጠራችኋቸው ስሞች ብቻ እንጅ ምንም አይደሉም፡፡ አላህ በእርሷ (መግገዛት) ምንም ማስረጃ አላወረደም፡፡ ከጌታቸውም መምሪያ የመጣላቸው ሲኾኑ ጥርጣሬንና ነፍሶች የሚዘነበሉበትን እንጅ ሌላ አይከተሉም፡፡
Verse 25
መጨረሻይቱም መጀመሪያይቱም (ዓለም) የአላህ ብቻ ናቸው፡፡
እነዚያ በመጨረሻይቱ ዓለም የማያምኑት መላእክትን በሴት አጠራር ይጠራሉ፡፡
ከግሣጼያችንም (ከቁርኣን) ከሸሸና አነስተኛይቱን ሕይወት እንጅ ሌላን ከማይሻ ሰው ዙር (ተወው)፡፡
ይህ (አነስተኛይቱን ሕይወት መምረጥ) ከዕውቀት ድካቸው ነው፡፡ ጌታህ እርሱ ከመንገዱ የተሳሳተውን በእርግጥ ዐዋቂ ነው፡፡ እርሱም የቀናውን ሰው ዐዋቂ ነው፡፡
በሰማያት ያለውና በምድር ያለው ሁሉ የአላህ ነው፡፡ እነዚያን ያጠፉትን በሠሩት ሊቀጣ እነዚያን ያሳመሩትንም በመልካሚቱ (ገነት) ሊመነዳ (የጠመመውንና የቀናውን ያውቃል)፡፡
(እነርሱ) እነዚያ የኃጢኣትን ታላለቆችና አስጸያፊዎቹን የሚርቁ ናቸው፡፡ ግን ትናንሾቹ የሚማሩ ናቸው፡፡ ጌታህ ምሕረተ ሰፊ ነውና፡፡ ከምድር በፈጠራችሁ ጊዜ እናንተም በእናቶቻችሁ ሆዶች ውስጥ ሽሎች በኾናችሁ ጊዜ እርሱ በናንተ (ኹነታ) ዐዋቂ ነው፡፡ ነፍሶቻችሁንም አታወድሱ እርሱ የሚፈራውን ሰው ዐዋቂ ነው፡፡
Verse 33
ያንን (ከእምነት) የዞረውን አየህን?
Verse 34
ጥቂትን የሰጠውንና ያቋረጠውንም (አየህን?)
የሩቁ ምስጢር ዕውቀት እርሱ ዘንድ አልለን? ስለዚህ እርሱ ያያልን?
ይልቁንም በዚያ በሙሳ ጽሑፎች ውስጥ ባለው ነገር አልተነገረምን?
Verse 37
በዚያም (የታዘዘውን) በፈጸመው በኢብራሂም (ጽሑፎች ውስጥ ባለው አልተነገረምን?)
(እርሱም ኃጢያት) ተሸካሚ ነፍስ የሌላይቱን ነፍስ ኃጢኣት አትሸከምም፡፡
Verse 41
ከዚያም ሙሉውን ምንዳ ይመነዳዋል፡፡
Verse 43
እነሆ እርሱም አስሳቀ፣ አስለቀሰም፡፡
እርሱም ሁለቱን ዓይነቶች ወንድንና ሴትን ፈጠረ፡፡
Verse 46
ከፍትወት ጠብታ (በማህጸን ውስጥ) በምትፈሰስ ጊዜ፡፡
Verse 47
የኋለኛይቱም ማስነሳት በእርሱ ላይ ነው፡፡
Verse 48
እነሆ እርሱም አከበረ፣ ጥሪተኛም አደረገ፡፡
Verse 50
እነሆ እርሱም የፊተኛይቱን ዓድ አጥፍቷል፡፡
Verse 51
ሰሙድንም (አጥፍቷል)፤ አላስቀረምም፡፡
በፊትም የኑሕን ሕዝቦች (አጥፍቷል)፡፡ እነርሱ በጣም በደለኞችና እጅግ የጠመሙ እነርሱ ነበሩና፡፡
Verse 53
የተገለበጠችውንም ከተማ ደፋ፡፡
Verse 55
ከጌታህም ጸጋዎች በየትኛው ትጠራጠራለህ?
ይህ ከፊተኞቹ አስፈራሪዎች (ጎሳ) የኾነ አስፈራሪ ነው፡፡
Verse 57
ቀራቢይቱ (ኅልፈተ ዓለም) ቀረበች፡፡
Verse 60
ትስቃላችሁምን? አታለቅሱምን?
Verse 61
እናንተም ዘንጊዎች ናችሁ፡፡
تقدم القراءة