سورة البروج

الترجمة الأمهرية

የሱራ البروج ትርጉም በالأمهرية ከالترجمة الأمهرية

الترجمة الأمهرية

Verse 1
የቡርጆች ባለቤት በኾነችው ሰማይ እምላለሁ፡፡
Verse 3
በተጣጅና በሚጣዱትም፤ (እምላለሁ)፡፡
Verse 4
የጉድቡ ባለቤቶች ተረገሙ፡፡
Verse 5
የማገዶ ባለቤት የኾነቺው እሳት (ባለቤቶች)፡፡
Verse 6
እነርሱ በርሷ (አፋፍ) ላይ ተቀማጮች በኾኑ ጊዜ፤ (ተረገሙ)፡፡
እነርሱም በምእምናኖቹ በሚሠሩት (ማሰቃየት) ላይ መስካሪዎች ናቸው፡፡
ከእነርሱም በአላህ አሸናፊው፣ ምስጉኑ በኾነው (ጌታ) ማመናቸውን እንጅ ሌላ ምንም አልጠሉም፡፡
በእዚያ የሰማያትና የምድር ንግሥና ለእርሱ ብቻ በኾነው (አላህ ማመናቸውን)፡፡ አላህም በነገሩ ሁሉ ላይ መስካሪ ነው፡፡
እነዚያ ምእምንንና ምእምናትን ያሰቃዩ፣ ከዚያም ያልተጸጸቱ ለእነርሱ የገሀነም ቅጣት አልላቸው፡፡ ለእነርሱም የመቃጠሉ ስቃይ አልላቸው፡፡
እነዚያ ያመኑና መልካም ሥራዎችንም የሠሩ ለእነርሱ ከሥሮቻቸው ወንዞች የሚፈሱባቸው ገነቶች አሏቸው፡፡ ይህ ታላቅ ማግኘት ነው፡፡
Verse 12
የጌታህ በኀይል መያዝ ብርቱ ነው፡፡
Verse 13
እነሆ እርሱ መፍጠርን ይጀምራል፤ ይመልሳልም፡፡
Verse 14
እርሱም ምሕረተ ብዙ ወዳድ ነው፡፡
Verse 15
የዙፋኑ ባለቤት የላቀው ነው፡፡
Verse 18
የፈርዖንና የሰሙድ፤ (ወሬ)፡፡
በእውነቱ እነዚያ የካዱት በማስተባበል ውስጥ ናቸው፡፡
Verse 20
አላህም በዙሪያቸው (በዕውቀቱ) ከባቢ ነው፡፡
Verse 21
ይልቁንም እርሱ የከበረ ቁርኣን ነው፡፡
Verse 22
የተጠበቀ በኾነ ሰሌዳ ውስጥ ነው፡፡
تقدم القراءة