سورة الفجر

الترجمة الأمهرية

የሱራ الفجر ትርጉም በالأمهرية ከالترجمة الأمهرية

الترجمة الأمهرية

Verse 1
በጎህ እምላለሁ፡፡
Verse 3
በጥንዱም በነጠላውም፡፡
Verse 7
በኢረም በባለ ረዣዢሚቱ አዕማድ፡፡
በዚያች ብጤዋ በአገሮች ውስጥ ያልተፈጠረ በኾነችው፡፡
በሰሙድም በእነዚያ በሸለቆው ቋጥኝን የቆረጡ በኾኑት፡፡
Verse 10
በፈርዖንም ባለ ችካሎች በኾነው፡፡
Verse 11
በእነዚያ በአገሮች ላይ ግፍ የሠሩ፡፡
Verse 12
በእርሷም ውስጥ ጥፋትን ያበዙ በኾኑት (እንዴት እንደሠራ አታውቅምን?)
በእነርሱ ላይም ጌታህ የቅጣትን አለንጋ አወረደባቸው፡፡
Verse 14
ጌታህ በመጠባበቂያ ላይ ነውና፡፡
ሰውማ ጌታው በሞከረው ጊዜ፣ ባከበረውና ባጣቀመውም (ጊዜ) «ጌታዬ አከበረኝ (አበለጠኝ)» ይላል፡፡
Verse 19
የውርስንም ገንዘብ የመሰብሰብን አበላል ትበላላችሁ፡፡
Verse 20
ገንዘብንም ብዙን መውደድ ትወዳላችሁ፡፡
መላእክትም ሰልፍ ሰልፍ ኾነው ጌታህ (ለሱ ክብር በምስማማ መልኩ) በመጣ ጊዜ፤
ገሀነምም በዚያ ቀን በተመጣች ጊዜ በዚያ ቀን ሰው (ጥፋቱን) ይገነዘባል፡፡ መገንዘብም ለእርሱ ከየቱ?
Verse 24
«ዋ እኔ! ምነው በሕይወቴ (መልካምን ሥራ) ባስቀደምኩ ኖሮ» ይላል፡፡
በዚያ ቀንም የርሱን አቀጣጥ አንድም አይቀጣም፡፡
Verse 26
የእርሱንም አስተሳሰር አንድም አያስርም፡፡
Verse 27
(ለአመነች ነፍስም) «አንቺ የረካሺው ነፍስ ሆይ!
«ወዳጅ ተወዳጅ ኾነሽ ወደ ጌታሽ ተመለሺ፡፡
Verse 30
ገነቴንም ግቢ፤» (ትባላለች)፡፡
تقدم القراءة