የሱራ الفجر ትርጉም በالأمهرية ከالترجمة الأمهرية
Verse 1
ﭤ
ﭥ
በጎህ እምላለሁ፡፡
Verse 2
ﭦﭧ
ﭨ
በዐሥር ሌሊቶችም፡፡
Verse 3
ﭩﭪ
ﭫ
በጥንዱም በነጠላውም፡፡
Verse 4
ﭬﭭﭮ
ﭯ
በሌሊቱም በሚኼድ ጊዜ፡፡
Verse 5
ﭰﭱﭲﭳﭴﭵ
ﭶ
በዚህ (መሓላ) ለባለ አእምሮ ታላቅ መሓላ አለበትን?
Verse 6
ﭷﭸﭹﭺﭻﭼ
ﭽ
ጌታህ በዓድ እንዴት እንደ ሠራ አታውቅምን?
Verse 7
ﭾﭿﮀ
ﮁ
በኢረም በባለ ረዣዢሚቱ አዕማድ፡፡
Verse 8
ﮂﮃﮄﮅﮆﮇ
ﮈ
በዚያች ብጤዋ በአገሮች ውስጥ ያልተፈጠረ በኾነችው፡፡
Verse 9
ﮉﮊﮋﮌﮍ
ﮎ
በሰሙድም በእነዚያ በሸለቆው ቋጥኝን የቆረጡ በኾኑት፡፡
Verse 10
ﮏﮐﮑ
ﮒ
በፈርዖንም ባለ ችካሎች በኾነው፡፡
Verse 11
ﮓﮔﮕﮖ
ﮗ
በእነዚያ በአገሮች ላይ ግፍ የሠሩ፡፡
Verse 12
ﮘﮙﮚ
ﮛ
በእርሷም ውስጥ ጥፋትን ያበዙ በኾኑት (እንዴት እንደሠራ አታውቅምን?)
Verse 13
ﮜﮝﮞﮟﮠ
ﮡ
በእነርሱ ላይም ጌታህ የቅጣትን አለንጋ አወረደባቸው፡፡
Verse 14
ﮢﮣﮤ
ﮥ
ጌታህ በመጠባበቂያ ላይ ነውና፡፡
Verse 15
ሰውማ ጌታው በሞከረው ጊዜ፣ ባከበረውና ባጣቀመውም (ጊዜ) «ጌታዬ አከበረኝ (አበለጠኝ)» ይላል፡፡
Verse 16
በሞከረውና በእርሱ ላይ ሲሳዩን ባጠበበ ጊዜማ «ጌታዬ አሳነሰኝ» ይላል፡፡
Verse 17
ﯞﯟﯠﯡﯢﯣ
ﯤ
ይከልከል፤ ይልቁንም የቲምን አታከብሩም፡፡
Verse 18
ﯥﯦﯧﯨﯩ
ﯪ
ድኻንም በማብላት ላይ አትታዘዙም፡፡
Verse 19
ﯫﯬﯭﯮ
ﯯ
የውርስንም ገንዘብ የመሰብሰብን አበላል ትበላላችሁ፡፡
Verse 20
ﯰﯱﯲﯳ
ﯴ
ገንዘብንም ብዙን መውደድ ትወዳላችሁ፡፡
Verse 21
ተዉ፤ ምድር ደጋግማ በተሰባበረች ጊዜ፤
Verse 22
ﯽﯾﯿﰀﰁ
ﰂ
መላእክትም ሰልፍ ሰልፍ ኾነው ጌታህ (ለሱ ክብር በምስማማ መልኩ) በመጣ ጊዜ፤
Verse 23
ገሀነምም በዚያ ቀን በተመጣች ጊዜ በዚያ ቀን ሰው (ጥፋቱን) ይገነዘባል፡፡ መገንዘብም ለእርሱ ከየቱ?
Verse 24
ﭜﭝﭞﭟ
ﭠ
«ዋ እኔ! ምነው በሕይወቴ (መልካምን ሥራ) ባስቀደምኩ ኖሮ» ይላል፡፡
Verse 25
ﭡﭢﭣﭤﭥ
ﭦ
በዚያ ቀንም የርሱን አቀጣጥ አንድም አይቀጣም፡፡
Verse 26
ﭧﭨﭩﭪ
ﭫ
የእርሱንም አስተሳሰር አንድም አያስርም፡፡
Verse 27
ﭬﭭﭮ
ﭯ
(ለአመነች ነፍስም) «አንቺ የረካሺው ነፍስ ሆይ!
Verse 28
ﭰﭱﭲﭳﭴ
ﭵ
«ወዳጅ ተወዳጅ ኾነሽ ወደ ጌታሽ ተመለሺ፡፡
Verse 29
ﭶﭷﭸ
ﭹ
«በባሮቼም ውስጥ ግቢ፡፡
Verse 30
ﭺﭻ
ﭼ
ገነቴንም ግቢ፤» (ትባላለች)፡፡
تقدم القراءة